Thursday, June 1, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርትየስፖርት አካዴሚው በቴኳንዶ ሥልጠና ሊሰጥ ነው

የስፖርት አካዴሚው በቴኳንዶ ሥልጠና ሊሰጥ ነው

ቀን:

 

የወርልድ ቴኳንዶ ስፖርት በ1970ዎቹ ውስጥ መጀመሩን የብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴ መረጃ ያመለክታል፡፡ ስፖርቱን ለማስፋፋት ብሔራዊ ፌዴሬሽኑ ወደ ተግባር ከገባ በ5 ዓመታት ውስጥ በአገሪቱ ስፖርቱን ለማስፋፋት በርካታ ስፖርተኞችንና ክለቦችን ሊፈሩ ችሏል፡፡ ለኢትዮጵያ ወርልድ ቴኳንዶ ፌዴሬሽን ትልቁ ስኬት በ2006 ዓ.ም. ኮንጎ ብራዛቪል ባዘጋጀችው 11ኛው የመላው አፍሪካ ጨዋታዎች ናርዶስ ሲሳይ የወርቅ ሜዳሊያ ማግኘት ነው፡፡ ከአትሌቲክስና ብስክሌት ቀጥሎ ቴኳንዶ በወርቅ መዝገብ ውስጥ ለመግባት ችሏል፡፡ የወርልድ ቴኳንዶ ስፖርትን በኢትዮጵያ ይበልጥ ለማስፋፋት እንዲያመች የኢትዮጵያ ወጣቶች ስፖርት አካዴሚ በአካዴሚው ውስጥ ሥልጠና ለመስጠት ከብሔራዊ ፌዴሬሽኑ ጋር የመግባቢያ ስምምነት አድርጓል፡፡ ነሐሴ 25 ቀን 2009 ዓ.ም. የጋራ መግባቢያ ሰነዱ የተፈረመው፣ ወጣቶች ለቴኳንዶ ስፖርት ያላቸው ዝንባሌ እንዲያድግ ለማድረግና በዚህ ደረጃ የሚሰጣቸው ሥልጠና ለከፍተኛ ደረጃ እንዲበቁ ለማድረግ ነው፡፡ ስምምነቱን የአካዴሚው ዋና ዳይሬክተር አቶ አምበሳው እንየውና የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት አቶ ዳዊት አስፋው ተፈራ (ፎቶ በቀኝ) ተፈራርመዋል፡፡ ስምምነቱ ለብሔራዊ ቡድን ቅድመ ዝግጅት ከመርዳቱም ባሻገር ባለሙያዎችን ለማፍራት እንደሚያስችል አቶ ዳዊት ተናግረዋል፡፡ (በዳዊት ቶሎሳ)

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በአዲስ አበባ በድምቀት ተከበረ

የአዛርባጃን ኤምባሲ  የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በትላንትናው ዕለት አከበረ። ሰኞ...

የመንግሥትና የሃይማኖት ልዩነት መርህ በኢትዮጵያ

እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አገሮች የሃይማኖት ተቋማት አዎንታዊ ሚና የጎላ...

ሐበሻ ቢራ ባለፈው በጀት ዓመት 310 ሚሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን አስታወቀ

የአንድ አክሲዮን ሽያጭ ዋጋ 2,900 ብር እንዲሆን ተወስኗል የሐበሻ ቢራ...