Tuesday, November 28, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናየአሥራ ሁለት አምባሳደሮች ምደባ ይፋ ሆነ

የአሥራ ሁለት አምባሳደሮች ምደባ ይፋ ሆነ

ቀን:

ፕሬዚዳንት ሙላቱ ተሾመ ሐምሌ 19 ቀን 2009 ዓ.ም. የሰጡት የአሥራ ሁለት አምባሳደሮች ሹመት ምደባ ይፋ ሆነ:: የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃለ አቀባይ ጽሕፈት ቤት በፌስቡክ ገጹ ይፋ እንዳደረገው፣ አምባሳደር ብርሃነ ገብረ ክርስቶስ አቶ ሥዩም መስፍንን ተክተው የቻይና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ሆነው ተመድበዋል:: አቶ ካሳ ተክለ ብርሃንም አቶ ግርማ ብሩን ተክተው የአሜሪካ ባለሙሉ ባለሥልጣን አምባሳደር ሆነዋል::

በተመሳሳይ የቀድሞ የሲቪል ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ሚኒስትር ወ/ሮ አስቴር ማሞ የካናዳ፣ የቀድሞው የትምህርት ሚኒስትር ሽፈራው ተክለ ማርያም (ዶ/ር) የደቡብ አፍሪካ፣ እንዲሁም የቀድሞ የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ የስዊዲን ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ሆነው ተመድበዋል::

ከዚህ በተጨማሪ አምባሳደር ተበጀ በርሄ የተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስ፣ አቶ መታሰቢያ ታደሰ የኳታር፣ የቀድሞው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር አድማሱ ፀጋዬ የኢንዶኔዥያ፣ ወ/ሮ ሉሊት ዘውዴ የሩዋንዳ፣ የሥነ ምግባር ፀረ ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ዓሊ ሱሌይማን የፈረንሣይ፣ እንዲሁም አቶ ሙሉጌታ ዘውዴ የሱዳን ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ሆነው ተመድበዋል::

የጠቅላይ ሚኒስትሩ ልዩ ረዳት የነበሩት አቶ እውነቱ ብላታ በብራሰልስ የአውሮፓ ኅብረት አምባሳደር መሆናቸው ታውቋል::

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ለሲኒመር ትሬዲንግ አ/ማ አባላት በሙሉ የጠቅላላ ጉባኤ የስብሰባ ጥሪ

ለሲኒመር ትሬዲንግ አ/ማ አባላት በሙሉ የጠቅላላ ጉባኤ የስብሰባ ጥሪ ሲኒመር ትሬዲንግ...

የባህር በር በቀጣናዊ ተዛምዶ ውስጥ

በበቀለ ሹሜ መግቢያ በ2010 ዓ.ም. መጋቢት ማለቂያን ይዞ ዓብይ አህመድ በጠቅላይ...

ሥጋት ያስቀራል ተብሎ የሚታሰበው የጫኝና አውራጅ መመርያ

በአዲስ አበባ ከተማ በሕገወጥ መልኩ በመደራጀት ማኅበረሰቡ ላይ እንግልትና...

ማወቅ ወይስ አለማወቅ – ድፍረት ወይስ ፍርኃት?

በአሰፋ አደፍርስ ወገኖቼ ፈርተንም ደፍረንም የትም አንደርስምና ለአገራችን ሰላምና ክብር...