Thursday, June 1, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናተቃዋሚ ፓርቲዎችና ኢሕአዴግ በቅርቡ መደራደር ሊጀምሩ ነው

ተቃዋሚ ፓርቲዎችና ኢሕአዴግ በቅርቡ መደራደር ሊጀምሩ ነው

ቀን:

ገዥው ፓርቲ ኢሕአዴግና 16 ተቃዋሚ ፓርቲዎች ከመጪው ሐምሌ 17 ቀን 2009 ዓ.ም. ጀምሮ ድርድር ለመጀመር ተስማሙ፡፡

ፓርቲዎቹ ዓርብ ሐምሌ 7 ቀን 2009 ዓ.ም. ለመደራደር በዘረዘሯቸው 12 ርዕሶች ላይ አምስት ሰዓታት የፈጀ ውይይት አካሂደዋል፡፡

ለድርድር ከዘረዘሯቸው 12 ነጥቦች የትኛው ቅድሚያ ይሰጠው በሚለው ላይ ታዛቢዎችን ያሰለቸ ውይይት ካደረጉ በኋላ፣ በመጨረሻ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ አዋጅ ቁጥር 573/2000 ቅድሚያ ተሰጥቶት ለድርድር እንዲቀርብ ወስነዋል፡፡

በቀጣይነትም የምርጫ አዋጅ ቁጥር 532/2000 ለድርድር እንዲቀርብ፣ በሦስተኛነት የፖለቲካ ፓርቲዎች የሥነ ምግባር አዋጅ፣ በአራተኛነት የፀረ ሽብርተኝነት አዋጁ በቅደም ተከተል ውይይት እንዲደረግባቸው ተስማምተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ራዕይ ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ ተሻለ ሰብሮ የመጀመሪያ የድርድር ርዕስ እንዲሆን በከፍተኛ ደረጃ የሞገቱበት ብሔራዊ መግባባት የሚለው ርዕስ፣ በመጨረሻ የድርድር አጀንዳነት እንዲቀመጥ በአብላጫ ድምፅ ተወስኗል፡፡

ድርድሩ ሐምሌ 17 ቀን ከመጀመሩ በፊት በሚውለው ሳምንት ማለትም  ከሰኞ ሐምሌ 10 ቀን እስከ ዓርብ ሐምሌ 14 ቀን 2009 ዓ.ም.፣ በፓርቲዎች የምዝገባ አዋጅ ላይ ሊሻሻሉ ይገባል የሚሏቸውንና የመፍትሔ ሐሳቦቻቸውን ዘረዝረው በጽሑፍ ለአደራዳሪ ኮሚቴ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡

አደራዳሪ ኮሚቴው በጽሑፍ የቀረቡለትን ዝርዝር ነጥቦች ለኢሕአዴግ በማቅረብ፣ ከሰኞ ሐምሌ 17 ቀን 2009 ዓ.ም. ጀምሮ መልስ በመስጠት ድርድሩን ለመጀመር ቀጠሮ ተይዟል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በአዲስ አበባ በድምቀት ተከበረ

የአዛርባጃን ኤምባሲ  የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በትላንትናው ዕለት አከበረ። ሰኞ...

የመንግሥትና የሃይማኖት ልዩነት መርህ በኢትዮጵያ

እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አገሮች የሃይማኖት ተቋማት አዎንታዊ ሚና የጎላ...

ሐበሻ ቢራ ባለፈው በጀት ዓመት 310 ሚሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን አስታወቀ

የአንድ አክሲዮን ሽያጭ ዋጋ 2,900 ብር እንዲሆን ተወስኗል የሐበሻ ቢራ...