- Advertisement -

የኦሮሚያ ክልል በተለያዩ ዘርፍ ያሠለጠናቸውን ከአንድ ሺሕ በላይ የፖሊስ መኮንኖችን አስመረቀ

የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሌጅ በወንጀል መከላከል፣ በምርመራ፣ በሥነ ምግባር መኮንንነት፣ በሥርዓተ ፆታ ጥቃት መከላከልና ማስቆም ለአንድ ዓመት ያሠለጠናቸውን 1,179 ፖሊስ መኮንኖች መጋቢት 15 ቀን 2009 ዓ.ም. አስመረቀ፡፡

የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ጄኔራል ኮሚሽነር ኢተፋ ቶላ በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር እንደገለጹት፣ በአገሪቱ እየተመዘገበ ያለውን የዕድገትና የልማት ቀጣይነት ለማረጋገጥ ሰላም ወሳኝ መሆኑንና ለዚህም የፖሊስ ኃላፊነት ቀዳሚ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ወንጀልን አስቀድሞ ለመከላከል የሚችል የፖሊስ ኃይል ለማፍራት ኮሚሽኑ የፖሊስ አባላትን በአቅም፣ በክህሎትና በአመለካከት ለመገንባት የጀመራቸውን ሥራዎች አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም ኮሚሽነሩ አክለዋል፡፡

የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ዑመር ሁሴን እንደገለጹት፣ ኅብረተሰቡ ትክክለኛ ፍትሕ እንዲያገኝና በፖሊስ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚታየውን የአቅም፣ የክህሎትና የአመለካከት ክፍተት ለመድፈን የክልሉ መንግሥት በትኩረት እየሠራ ነው፡፡

የሕዝቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ በሚደረገው እንቅስቃሴ ውስጥ፣ የፖሊስ ሠራዊት አባላት ሚና ከፍተኛ እንደሆነም ገልጸዋል፡፡

አቶ ዑመር እንዳሉት፣ የፖሊስን የአገልግሎት አሰጣጥ ወደ አዲስ ምዕራፍ ለማሸጋገር፣ ሳይንስን መሠረት ባደረገ መንገድ የአባላቱን አቅም ለመገንባት የክልሉ መንግሥት ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ ይገኛል፡፡

በዕውቀት፣ በክህሎትና በአመለካከት ከዘመኑ ቴክኖሎጂ ጋር የተዋሀደ የፖሊስ ሠራዊት ለማፍራት የተጀመረው ሥልጠናና የአቅም ግንባታ ሥራም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ምክትል ፕሬዚዳንቱ አክለዋል፡፡

- Advertisement -

የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሌጅ ዳይሬክተር ረዳት ኮሚሽነር አበበ ለገሰ በበኩላቸው፣ ሥልጠናውን ወስደው ወደ ተግባር የሚገቡ የፖሊስ ሠራዊት አባላት፣ ኅብረተሰቡ በፍትሕ ዘርፍ የሚያነሳውን ቅሬታ ለመፍታት ጠንክረው መሥራት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል፡፡

ኮሌጁ በፖሊስ አገልግሎት ላይ የሚታየውን ክፍተት ለማጥበብና በሙያዊ ሥነ ምግባር የታነፀ የፖሊስ ኃይል በጥራትና በብዛት ለማፍራት፣ ከ2010 ዓ.ም. ጀምሮ በዲግሪ መርሐ ግብር ማሠልጠን እንደሚጀምር ጠቁመዋል፡፡

ሥልጠናው የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥና በፖሊስ ሳይንስ መሠረት ለመሥራት፣ ዕውቀትና ክህሎት ያገኙበት መሆኑን ተመራቂዎቹ ተናግረዋል፡፡  

- Advertisement -

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን

ከ ተመሳሳይ አምዶች

ሕወሓትን አጣብቂኝ ውስጥ የከተተው መመርያ

በሁለት አንጃ ተከፍሎ የእርስ በርስ የቃላት ጦርነት ውስጥ የገባው ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) ልዩነቱን ትቶ ወደቀድሞው አንድነቱ በመመለስ የሚጠበቅበትን ጠቅላላ ጉባዔ የማድረግ አልያም...

የትግራይ ክልል ተፈናቃዮች የኢትዮጵያ ሕዝብ ወደ ቀዬአችን እንድንመለስ ድምፅ ይሁነን ሲሉ ጠየቁ

ከሰኞ ጥር 5 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ ለሦስት ቀናት የተቃውሞ ሠልፍ በመቀሌ ከተማ እያካሄዱ ያሉት የትግራይ ክልል ተፈናቃዮች፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ ድምፅ እንዲሆናቸው ጠየቁ፡፡ በፕሪቶሪያ...

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በታጣቂዎችና ሚሊሻዎች መካከል በተከፈተ ተኩስ የሰዎች ሕይወት ማለፉ ተገለጸ

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በመተክል ዞን ቡለን ከተማ፣ በሸኔ ታጣቂዎችና በክልሉ ሚሊሻዎች መካከል በተከፈተ ተኩስ የሰው ሕይወት መጥፋቱ ተሰማ፡፡ የክልሉ ነዋሪዎች ‹‹የሸኔ ኃይሎች›› በማለት ወደ የጠሯቸው...

መንግሥትና ታጣቂዎች በየትኛውም ቦታና ሰዓት ለመነጋገር ዝግጁ ሲሆኑ ለማገዝ ዝግጁ መሆኗን አሜሪካ አስታወቀች

የሲቪክ ምኅዳሩ ሊጠበቅና ሚዲያዎች በነፃነት ሊሠሩ ይገባል ተብሏል ‹‹በአማራና በኦሮሚያ ክልሎች መንግሥትና ታጣቂዎች ገንቢ በሆነ መንገድ በየትኛውም ቦታና ጊዜ ሰላማዊ ንግግር ለማድረግ ዝግጁ ሲሆኑ ለማገዝ...

መንግሥት ባለፉት አምስት ዓመታት 1.5 ሚሊዮን ቤቶችን ገንብቻለሁ አለ

የንብረት ታክስ አዋጅ እምብዛም ማስተካከያ ሳይደረግበት መፅደቁ ቅሬታ ፈጥሯል መንግሥት ኢሕአዴግ መንግሥት ሆኖ አገሪቷን ሲያስተዳድር ለ14 ዓመታት (ከ1996 እስከ 2010 ዓ.ም.) በአገሪቱ ከገነባቸው ኮንዶሚኒየም የጋራ...

በነዳጅ ማደያዎች የቴሌብር ወኪሎች እንዲነሱ ትዕዛዝ ተላለፈ

በዮናታን ዮሴፍ ካለፈው ሳምንት ጀምሮ በሁሉም የነዳጅ ማደያዎች ሲሠሩ የነበሩ የቴሌብርም ሆነ የማደያ ወኪሎች እንዲነሱ ሲል የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን ለሁሉም የነዳጅ አከፋፋይ ኩባንያዎች፣ ለኢትዮ ቴሌኮምና...

አዳዲስ ጽሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ ቀኑን ሙሉ ከዋሉበት የሥራ አስፈጻሚ ስብሰባ ወደ መኖሪያ ቤታቸው ተመልሰው ከባለቤታቸው ጋር እያወጉ ነው]

የምን ስብሰባ ላይ ዋልኩ ነበር ያልከኝ? የሥራ አስፈጻሚ። የምን ሥራ አስፈጻሚ? የገዥው ሥራ አስፈጻሚ። ምን ገጥሟችሁ ነው የተሰበሰባችሁት? ለመረጠን ሕዝብ ቃል የገባናቸውን ተግባራት አፈጻጸም የምንገመግምበት የተለመደ ስብሰባ ነው። የገባችሁት ቃል...

ሕወሓትን አጣብቂኝ ውስጥ የከተተው መመርያ

በሁለት አንጃ ተከፍሎ የእርስ በርስ የቃላት ጦርነት ውስጥ የገባው ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) ልዩነቱን ትቶ ወደቀድሞው አንድነቱ በመመለስ የሚጠበቅበትን ጠቅላላ ጉባዔ የማድረግ አልያም...

ባንኮች እየፈጸሙት ያለው አቅርቦትንና ፍላጎትን ያላገናዘበ የውጭ ምንዛሪ ግዥ

የውጭ ምንዛሪ ግብይት በገበያ ዋጋ እንዲገበይ የወጣው ሕግ ተግባራዊ መሆን ከጀመረ ከሰባት ወራት በላይ አስቆጥሯል፡፡ ሕጉ ተግባራዊ በተደረገበት የመጀመርያው ቀን የአንድ ዶላር የምንዛሪ ዋጋ...

አሳረኛው ኑሮ!

የዛሬው ጉዞ ከቦሌ ወደ ፒያሳ ይሆን ዘንድ ግድ ሆኗል፡፡ ለምን? በኑሮ  ምክንያት፡፡ የታክሲ መሠለፊያው ወሬ የነዳጅ ጭማሪውን ተከትሎ ስለሚመጣው ተጨማሪ ታሪፍ ነው፡፡ ‹‹የእኛ ኑሮ...

የግለሰቦች ለመብታቸው ኃላፊነት አለመውሰድ ለአገር ያለው አደጋ

በያሬድ ኃይለመስቀል አንድ የማከብረው ኢኮኖሚስት አንድ መጽሐፍ እንዳነብ መራኝና ማንበብ ጀመርኩኝ። ይህንን መጽሐፍ ሳነበው ከዋናው ሐሳብ ወጣ ብሎ ስለ “የነፃ ተጓዦች ሀተታ” (The Free Rider...

‹‹የብድርና ቁጠባ ኅብረት ሥራ ማኅበራትን ኢኮኖሚያዊ አስተዋጽኦ ማጠናከር ያስፈልጋል›› አቶ ፍፁም አብርሃ፣ የአሚጎስ ብድርና ቁጠባ ኅብረት ሥራ ማኅበር መሥራችና ሥራ አስኪያጅ

አሚጎስ የብድርና ቁጠባ ኅብረት ሥራ ማኅበር ከተመሠረተ አሥራ ሁለት ዓመታት ሆኖታል፡፡ በእነዚህ ዓመታት 8,500 አባላትን ማፍራት ችሏል፡፡ አሚጎስ ስለተመሠረተበት ዓላማ፣ እያከናወናቸው ስለሚገኙ ተግባራት፣ የብድርና...
[the_ad id="124766"]

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን