- Advertisement -

ሚድሮክ ቴክኖሎጂ ግሩፕ በቢሾፍቱ ከተማ አዲስ የፓኬጂንግ ፋብሪካ ሥራ አስጀመረ

በሚድሮክ ቴክኖሎጂ ግሩፕ ሥር የሚገኘው ብሉ ናይል የፖሊፕሮፕሊንና ክራፍት ከረጢት ማምረቻ ኩባንያ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ99 ሚሊዮን ብር ሐራጅ የገዛውን ፓኬጂንግ ፋብሪካ፣ አራት ሚሊዮን ብር ተጨማሪ ወጪ በማድረግ ሙሉ ዕድሳት አካሂዶ ሥራ አስጀመረ፡፡

ቅዳሜ ሐምሌ 15 ቀን 2009 ዓ.ም. ፋብሪካው በሚገኝበት በቢሾፍቱ ከተማ በተካሄደው የምረቃ ሥነ ሥርዓት አዲሱ ፓኬጂንግ ፋብሪካ፣ ‹‹ብሉ ናይል የፖሊፕሮፕሊንና ክራፍት ከረጢት ማምረቻ ኩባንያ ቁርቁራ ቅርንጫፍ›› ተብሎ ተሰይሟል፡፡

በህንድ ባለሀብቶች የተገነባው ኢኖቫ ፓኬጂንግ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የተበደረውን ብድር መመለስ ባለመቻሉ፣ ባንኩ ብድሩን ለማስመለስ ፋብሪካውን በሐራጅ ጨረታ ለብሉ ናይል ሸጦታል፡፡

ብሉ ናይል ለዚህ ፋብሪካ ተጨማሪ አራት ሚሊዮን ብር ወጪ በማድረግ ዕድሳቱን አጠናቆ፣ ቅዳሜ ሐምሌ 15 ቀን 2009 ዓ.ም. አስመርቆ ሥራ አስጀምሯል፡፡

በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የሚድሮክ ቴክኖሎጂ ግሩፕ ቺፍ ኤግዚኪዩቲቭ ኦፊሰር አረጋ ይርዳው (ዶ/ር)፣ የቀድሞው ኢኖቫ ፓኬጂንግ በሽያጭ ወደ ሚድሮክ ቴክኖሎጂ ግሩፕ ከተዛወረ በኋላ የብሉ ናይል የፖሊፕሮፕሊንና ክራፍት ከረጢት ማምረቻ ኩባንያ ‹‹ቁርቁራ ቅርንጫፍ›› ተብሎ እንዲቀጥል መደረጉን፣ የቀድሞ ሠራተኞች የሥራ ዋስትናቸው ተረጋግጦ በሥራ ገበታቸው ላይ እንዲቀጥሉ መደረጉን ተናግረዋል፡፡

ቺፍ ኤግዚኪዩቲቭ ኦፊሰሩ ጨምረው እንደገለጹት፣ ፋብሪካውን ሥራ ለማስጀመር በተካሄደው ጥገናና የማሻሻል ሥራ ሙሉ በሙሉ በሚድሮክ ቴክኖሎጂ ግሩፕ ባለሙያዎች ተከናውኖ መጠናቀቁም አስደስቷቸዋል፡፡

- Advertisement -

‹‹በኮንትራት ሲያገለግሉ የነበሩ የፋብሪካው 72 ሠራተኞች ቋሚ ሠራተኞኛ እንዲሆኑ ተደርጓል፤›› ሲሉ አክለው ገልጸዋል፡፡

በዕለቱ በተካሄደው የምረቃ ሥነ ሥርዓት ላይ የተገኙት የቢሾፍቱ ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ ጁላ ለማ፣ ሚድሮክ ቴክኖሎጁ ግሩፕ በቢሾፍቱ ከተማ ብዙ ኢንቨስተሮች ባልገቡበት ወቅት ሰፋፊ ኢንቨስትመንቶችን የጀመረ የከተማው ባለውለታ ነው ብለዋል፡፡

‹‹በቀጣይም የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ከሚድሮክ ቴክኖሎጂ ግሩፕ ኩባንያዎች ጋር በይበልጥ ተባብሮ ይሠራል፤›› በማለት ምክትል ከንቲባው ተናግረዋል፡፡

በሚድሮክ ቴክኖሎጂ ግሩፕ ሥር 25 ኩባንያዎች የሚገኙ ሲሆን፣ ከእነዚህ ውስጥ ሰባት ኩባንያዎች በቢሾፍቱና አካባቢው በተለያዩ የኢንቨስትመንት ሥራዎች ላይ ተሰማርተዋል፡፡

የብሉ ናይል የፖሊፕሮፕሊንና ክራፍት ከረጢት ማምረቻ ቁርቁራ ቅርንጫፍ፣ የማዳበሪያ ከረጢቶች፣ ብትን ጆንያዎችንና የዕቃ ማሸጊያ ፕላስቲኮችን ያመርታል፡፡ 

- Advertisement -

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን

ከ ተመሳሳይ አምዶች

መቶኛ ዓመቱን እያከበረ ያለው ጎንደር ዩንቨርስቲ  40ኛ ዙር የሕክምና ተማሪዎቹን አስመረቀ 

ጎንደር ዩኒቨርሲቲው  ዛሬ የካቲት 8 ቀን 2017 ዓ.ም ፣ 254 ወንድ እና 112 ሴት   የሕክምና ተማሪዎቹን ያስመረቀው ለ40ኛ ጊዜ መሆኑንና ይኸም ዩኒቨርስቲው የተመሠረተበትን ምዕተዓመት...

የተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች መንግስት የ60 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ሰጠ

በኢትዮጵያ ለዐይነ ስውራን ትምህርት መሠረተ ልማት የሚውል  የ60 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ  ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መንግስት ዛሬ የካቲት 8 ቀን 2017 ዓም መሰጠቱ ታወቀ። ድጋፉ የተሰጠው ...

ህወሓት ህጋዊ የፖለቲካ ፓርቲ ፈቃዱ ታገደ

-የቦርድ ትእዛዝ አክብሮ ካልተገኘ ከሶስት ወር በኋላ እንደሚሰረዝ ተገልጿል የምስረታ 50ኛ በዓሉን ለማክበር ቀናት የቀሩት ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ እንዳያደርግ ህጋዊ ፈቃዱ...

የአየር መንገዱን አሠራር ጥሰዋል በተባሉ የአዲስ አበባ ሽያጭ ቢሮ ሠራተኞች ላይ ዕርምጃ መወሰዱ ተገለጸ

- የሕግ ክፍሉ ክስ መመሥረት የሚቻልባቸውን ሁኔታዎች እየተመለከተ ነው ተብሏል ከኢትዮጵያ አየር መንገድ የማስታወቂያና የሕዝብ ግንኙነት የሥራ ክፍሎች ዕውቅና ውጪ፣ በቅጥር ግቢው ውስጥ የፎቶና የቪዲዮ...

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በውክልና ለግሉ ዘርፍ ለማስተላለፍ ያቀዳቸው አገልግሎቶች

የከተማው አስተዳደር ካቢኔ ሰሞኑን ባሳለፈው ውሳኔ የተመረጡ መንግሥታዊ አገልግሎቶችን በሦስተኛ ወገን ለማሠራት የሚያስችለውን ደንብ በማፅደቅ ተግባራዊ እንቅስቃሴ መጀመሩ ታውቋል፡፡  አስተዳደሩ ደንቡን ከማጽደቁ አስቀድሞ በሦስተኛ ወገን...

አይኤምኤፍ ብሔራዊ ባንክ ገለልተኛ ሆኖ እንዲሠራ ከመንግሥት ባለሥልጣናት ጋር ስምምነት ላይ መደረሱን ይፋ አደረገ

‹‹ማዕከላዊ ባንክ ውሳኔዎቹን በመረጃ ላይ ብቻ ተመሥርቶ ካላሳለፈ አገሪቱንም ሆነ ኢኮኖሚውን አይጠቅምም›› ክርስታሊና ጆርጂዬቫ፣ የአይኤምኤፍ ማኔጂንግ ዳይሬክተር የዓለም የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ...

አዳዲስ ጽሁፎች

መቶኛ ዓመቱን እያከበረ ያለው ጎንደር ዩንቨርስቲ  40ኛ ዙር የሕክምና ተማሪዎቹን አስመረቀ 

ጎንደር ዩኒቨርሲቲው  ዛሬ የካቲት 8 ቀን 2017 ዓ.ም ፣ 254 ወንድ እና 112 ሴት   የሕክምና ተማሪዎቹን ያስመረቀው ለ40ኛ ጊዜ መሆኑንና ይኸም ዩኒቨርስቲው የተመሠረተበትን ምዕተዓመት...

የተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች መንግስት የ60 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ሰጠ

በኢትዮጵያ ለዐይነ ስውራን ትምህርት መሠረተ ልማት የሚውል  የ60 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ  ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መንግስት ዛሬ የካቲት 8 ቀን 2017 ዓም መሰጠቱ ታወቀ። ድጋፉ የተሰጠው ...

ህወሓት ህጋዊ የፖለቲካ ፓርቲ ፈቃዱ ታገደ

-የቦርድ ትእዛዝ አክብሮ ካልተገኘ ከሶስት ወር በኋላ እንደሚሰረዝ ተገልጿል የምስረታ 50ኛ በዓሉን ለማክበር ቀናት የቀሩት ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ እንዳያደርግ ህጋዊ ፈቃዱ...

የአየር መንገዱን አሠራር ጥሰዋል በተባሉ የአዲስ አበባ ሽያጭ ቢሮ ሠራተኞች ላይ ዕርምጃ መወሰዱ ተገለጸ

- የሕግ ክፍሉ ክስ መመሥረት የሚቻልባቸውን ሁኔታዎች እየተመለከተ ነው ተብሏል ከኢትዮጵያ አየር መንገድ የማስታወቂያና የሕዝብ ግንኙነት የሥራ ክፍሎች ዕውቅና ውጪ፣ በቅጥር ግቢው ውስጥ የፎቶና የቪዲዮ...

[ክቡር ሚኒስትሩ የካቢኔ አባል የሆነ አንድ የተቃዋሚ ፓርቲ ተወካይ ስልክ ደውሎላቸው ሰሞኑን በተካሄደው ድርጅታዊ ጉባዔ ዙሪያ እያወሩ ነው]

ሰላም ክቡር ሚኒስትር፡፡ ሰላም ሰላም፣ እንዴት ነህ? ቢዘገይም እንኳን አደረስዎት ክቡር ሚኒስትር። ለምኑ? ለፓርቲዎ ሁለተኛ መደበኛ ጉባዔ እንኳን አደረስዎት ማለቴ ነው። ቆየ እኮ ከተጠናቀቀ? አስቀድሜ ቢዘገይም ያልኩት እኮ ለዚያ ነው...

የጋዛ ውዝግብ በአፍሪካ ቀንድ ላይ የደቀነው ሥጋት

የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ አማችና የቀድሞ የመካከለኛው ምሥራቅ የፖሊሲ አማካሪያቸው ጄርድ ኩሽነር፣ ከአሥር ወራት በፊት ነበር ፍልስጤሞችን ከጋዛ አንስቶ ሌላ ቦታ ስለማስፈር በይፋ ሲናገር...
[the_ad id="124766"]

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን