Saturday, April 1, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

[የክቡር ሚኒስትሩ የአክስት ልጅ ስልክ ደወለችላቸው]

[የክቡር ሚኒስትሩ የአክስት ልጅ ስልክ ደወለችላቸው]

  • ሄሎ፡፡
  • ሄሎ ጋሼ!
  • ማን ልበል?
  • እንዴ ድምፄን ረሳኸው?
  • ሴትዮ ስልኩን ልዘጋው ነው፡፡
  • የእታባ ልጅ ነኝ ጋሼ፡፡
  • እንዴ ከየት ተገኘሽ ዛሬ?
  • ብዙ ጊዜ ልደውል አስባለሁ ግን ሥራ ይበዛብሃል እያልኩ ነው፡፡
  • ለነገሩ አሁንም ቢዚ ነኝ፡፡
  • አውቃለሁ ጋሼ፡፡
  • ምን ፈልገሽ ደወልሽ?
  • አንድ ነገር ላማክርህ ብዬ ነው፡፡
  • ምንድን ነው የምታማክሪኝ?
  • ውጭ እንዴት ልሂድ ልልህ ነው?
  • ያው በደላላ ነዋ፡፡
  • እኔማ በጣም ስለመመረኝ በእግሬ ልጀምረው ነው፡፡
  • ምን ሆነሽ ተማረርሽ?
  • ሁሉ ነገር ያማርራል፡፡
  • ሥራ እየሠራሽ አይደል እንዴ?
  • እሱማ ለነገሩ ጀማምሬ ነበር፡፡
  • ታዲያ ምን ጎደለሽ?
  • በቃ ምቀኛ መንግሥት ካለ መሥራት አይቻልም፡፡
  • እየተሳደብሽ እኮ ነው?
  • ምን ላድርግ ወድጄ አይደለም፡፡
  • ምን ገጠመሽ?
  • ያው ቡና ጠጡ ብዬ ትንሽ ንግድ ቢጤ ጀምሬ ነበር፡፡
  • እሺ?
  • እና ትንሽ እንቀሳቀስ ነበር፡፡
  • ስለዚህ አንቺና ልጅሽን ነፃ አውጥተሻል ማለት ነው?
  • እሱማ በሚገባ፡፡
  • ታዲያ አሁን ምን ገጠመሽ?
  • ግብር የሚሉት ጣጣ፡፡
  • በግብር ቀልድ የለም፡፡
  • መጀመሪያ ማን ሲያስቀልድህ ጋሼ?
  • እንዴት?
  • በግብር ያማርሩሃል እንጂ አያስቀልዱህም፡፡
  • አልገባኝም?
  • ይኸው በቀን ሁለት ሺሕ ብር ትሸጫለሽ ብለው አመጡብኝ፡፡
  • ምን?
  • ቁጥር አያውቁም ስልህ?
  • ከቡና በቀን ሁለት ሺሕ ብር?
  • አይገርምህም ጋሼ?
  • እኔም አሁኑኑ ነው የምጀምረው፡፡
  • ምኑን?
  • ኑ ቡና ጠጡ!

[የክቡር ሚኒስትሩ የወንድም ልጅ ደወለላቸው]

  • ሄሎ ጋሼ፡፡
  • እንዴት ነህ ጎረምሳው?
  • አለሁ ጋሼ፡፡
  • ምነው ድምፅህ?
  • ምን ባክህ ሙዴ ተከንቶ ነው፡፡
  • አንተ ልጅ ይኼን ቋንቋ ተው አልተባልክም?
  • በቅርቡ የሥራ ቋንቋ ሊሆን ይችላል ብዬ ነው፡፡
  • ይኼን ፖለቲካህን እዛው፡፡
  • ጋሼ በጣም ተማርሬያለሁ፡፡
  • ምነው?
  • ሱቄን መቼም ታውቃታለህ?
  • ያቺ የክብሪት ቤት የምታክለው?
  • ጎሽ ጋሼ፡፡
  • ምን ሆነች?
  • አሁን እዛ ቤት በቀን ሰባት ሺሕ ብር ይሸጣል?
  • ምን አልከኝ?
  • በቀን ሰባት ሺሕ ትሸጣለህ አሉኝ እኮ ነው የምልህ?
  • ምን  ትቀልዳለህ?
  • እውነት ጋሼ፡፡
  • በእርግጥ ስንት ትሸጣለህ?
  • ሦስትም፣ አራትም አንዳንዴ እስከ አሥርም ይደርሳል፡፡
  • እ. . .
  • መንግሥት ግን ያለ ግብር አያውቅም እንዴ?
  • እና አሁን ምን ልታደርግ ነው?
  • እኔማ ልመልሰው እያሰብኩ ነው፡፡
  • ምኑን?
  • የንግድ ፈቃዴን፡፡
  • በቃ እኔ መፍትሔ አለኝ፡፡
  • ምን ልታደርግ?
  • እኔ እወስደዋለሁ፡፡
  • ምኑን?
  • ንግድ ፈቃዱን!

[የክቡር ሚኒስትሩ የእህት ልጅ ስልክ ደወለችላቸው]

  • ሄሎ ጋሼ፡፡
  • እሺ አንቺ ሞልቃቃ፡፡
  • እንዴት ነህ ጋሼ?
  • ዛሬ ግን እንዴት ነው የዘመድ ስልክ በዛብኝ?
  • ማን ደውሎልህ ነበር?
  • የአጎትሽ ልጅም ደውሎልኝ ነበር፡፡
  • እኔ እንኳን አንድ ነገር ልጠይቅህ ፈልጌ ነው፡፡
  • ምን ልጠይቂኝ?
  • ይኼ ግብርና ምናምን የሚሉት ነገር ምንድነው?
  • የምን ግብርና ነው?
  • ይኼ ገቢዎች የሚሉት ድርጅት ነዋ፡፡
  • ግብር ማለትሽ ነው?
  • አዎን ጋሼ፡፡
  • ምን ሆንሽ አንቺ ደግሞ?
  • ያው ቦሌ ላይ ሞባይል ቤት እንዳለኝ ታውቃለህ?
  • ከአንቺ አይደል እንዴ አይፎን የገዛሁት?
  • በቃ እየውልህ ጋሼ እኔ ብራንድ አይፎን ብቻ ነው የምይዘው፡፡
  • እሺ?
  • እና ይኸው ግብርና ምናምን ሊያመጡብኝ ነው፡፡
  • ግብር ነው የሚባለው አልኩሽ እኮ፡፡
  • ለመሆኑ በቀን ስንት ገመቱብሽ?
  • እኔ ጋ አልመጡም ግን ጓደኞቼን 20 ሺሕ ምናምን ብለዋቸዋል፡፡
  • ምን?
  • እና ጋሼ አስቁማቸው፡፡
  • በቃ አስቆማቸዋለሁ!

[የክቡር ሚኒስትሩ ሚስት ስልክ ደወሉ]

  • አቤት፡፡
  • ምን ለመሆን ፈልጋችሁ ነው ግን?
  • ማለት?
  • ሰላም አትፈልጉም እንዴ?
  • ከፀረ ሰላም ኃይሎች ጋር ዋልሽ መሰለኝ?
  • እናንተ ትመስሉኛላችሁ ፀረ ሰላሞቹ?
  • ሴትዮ እየተሳደብሽ ነው?
  • ሐሳባችሁ ግራ አጋብቶኝ ነው እኮ?
  • የምን ሐሳብ?
  • ይኸው ሰው ከሳዑዲ ዓረቢያ እንዲመጣ ትማፀናላችሁ?
  • ሰው አገር እንዳይሰቃዩ ነው እኮ፡፡
  • ታዲያ እኔ እዚሁ ለእነሱ የሥራ ዕድል ፈጠርኩ፡፡
  • እሱማ ጥሩ ነገር ነው ያደረግሽው፡፡
  • ይኸው መንግሥት ግን እየበጠበጠኝ ነው፡፡
  • እንዴት ማለት?
  • ፀጉር ቤቴ ሊዘጋ ነው፡፡
  • ለምን?
  • ሠራተኞቹም ሊበተኑ ነው፡፡
  • ማን አባቱ ነው የሚበትናቸው?
  • የተጠየኩት ግብር ነዋ፡፡
  • አልገባኝም?
  • በቀን ሰባት ሺሕ ትሠሪያለሽ ነው ያሉኝ፡፡
  • ታዲያ እንደዛ ከተሠራበት ለምን ሁሉም አይከፍቱም?
  • እኔ ምን አውቅላቸዋለሁ?
  • ተያቸው አሁን የመጡት በእንትኔ ነው፡፡
  • በምንህ?
  • በህልውናዬ!

[ለክቡር ሚኒስትሩ አንድ ደላላ ደወለላቸው]

  • ክቡር ሚኒስትር ሰሞኑን ከትልልቅ ሰዎች ጋር ስገናኝ ነበር፡፡
  • በምን ጉዳይ?
  • ለአገሪቱ ዕድገት ወሳኝ ነገር ላይ ስወያይ ነበር፡፡
  • ምን ዓይነት ነገር ነው?
  • ሱፐር ኮምፒዩተር ይባላል፡፡
  • ምንድነው እሱ?
  • ኮምፒዩተር ነው፡፡
  • ታዲያ ኮምፒዩተር አለን አይደል እንዴ?
  • ይኼኛው ሱፐር ነዋ፡፡
  • እህ. . .
  • ያው ዘመኑ የአይቲ አይደል?
  • በትክክል እንጂ፡፡
  • ስለዚህ ይኼን ኮምፒዩተር አገሪቷ መግዛት አለባት፡፡
  • ምን እናደርግበታለን ግን?
  • የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ዳታ በሙሉ ይቀመጥበታል፡፡
  • በጣም አሪፍ፡፡
  • ዋናው ነገር እሱ አይደለም፡፡
  • ታዲያ ምንድነው?
  • ከግዥው ከፍተኛ ኮሚሽን እናገኝበታለን፡፡
  • እውነት?
  • አዎ ኮሚሽናችን ውጭ እንዲቀመጥ ተስማምቻለሁ፡፡
  • በምን?
  • በዶላር!

[ክቡር ሚኒትሩ ኮምፒዩተሩን ገዝተው የአይቲ ክፍል ኃላፊውን አስጠሩት]

  • አቤት ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • አንድ ኮምፒዩተር አስገዝቻለሁ፡፡
  • አለዎት አይደል እንዴ?
  • ለእኔ አይደለም፡፡
  • ታዲያ ለማን ነው?
  • ለአገሪቷ፡፡
  • ለአገሪቷ?
  • አዎን ለአገሪቷ፡፡
  • ምን ሊያደርግላት?
  • ስማ ለዚህች  አገር መስዋዕትነት መክፈላችንን  ታውቃለህ?
  • እሱማ ሁላችንም ከፍለናል፡፡
  • እኛ እኮ አጥንታችንን ከስክሰን ደማችንን አፍስሰናል፡፡
  • አውቃለሁ፡፡
  • ስለዚህ እቺ አገር በጠላት እንድትጠቃ አልፈልግም፡፡
  • ማን ሊያጠቃት ነው?
  • የዚህ ዘመን ጦርነት እኮ በኮምፒዩተር ሆኗል፡፡
  • እና ምን እያሉኝ ነው?
  • ይኸው ተመልከተው፡፡

[ክቡር ሚኒስትሩ ሱፐር ኮምፒዩተሩ የተጫነበትን ኮንቴይነር ፎቶ በስልካቸው አሳዩት]

  • እየቀለዱ ነው ክቡር ሚኒስትር?
  • የምን ቀልድ ነው?
  • እና ኮምፒዩተሩ ተገዝቷል?
  • እህሳ፡፡
  • እኔንና ሌሎች የአይቲ ባለሙያዎችን ሳያማክሩ?
  • አንተን ማን አለቃ አደረገህ?
  • ምን?
  • ይኼ እኮ የዕድገታችን መገለጫ ነው፡፡
  • ይህ ዕድገት ሳይሆን. . .
  • እ. . .
  • ብክነት ነው!

[ክቡር ሚኒስትሩ አማካሪያቸውን አስጠሩት]

  • አቤት ክቡር ሚኒስትር?
  • ወዳጃችን ያደረገውን ሰማህ?
  • ማን ነው ወዳጃችን?
  • ፕሬዚዳንት ሮበርት ሙጋቤ ነዋ፡፡
  • ምን አደረገ?
  • የኅብረቱን ስብሰባ እየተከታተልክ አይደለም እንዴ?
  • ኧረ ነው፡፡
  • ይኸው አንድ ሚሊዮን ዶላር የሚያወጡ ከብቶችን ለገሰ እኮ፡፡
  • ለግድቡ ነው?
  • አንተ ደግሞ ሰፋ አድርገህ አስብ እንጂ?
  • እ. . .
  • ለኅብረቱ ነው፡፡
  • እሱንማ ሰምቻለሁ፡፡
  • ከብቶቹ በሰላም እንዴት እንደሚመጡ ሳስብበት ነበር፡፡
  • ምን አሉኝ?
  • ሎጂስቲክስ ላይ የሚሠራ ዘመድ አለኝ፡፡
  • እሺ?
  • እሱ እዚህ ድረስ ያመጣቸዋል፡፡
  • እሺ?
  • እዚህ ሲደርሱ የሚጠበቃቸው እረኛ አዘጋጅቻለሁ፡፡
  • ማንን?
  • አንድ ጥሩ እረኛ ዘመድ አለኝ፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር እርስዎም ግን ያስፈልግዎታል፡፡
  • ምን?
  • እረኛ!

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

በማኅበር ቤት ለመሥራት ለተመዘገቡ ቆጣቢዎች በቅርቡ ዕጣ  እንደሚወጣ ተገለጸ

ተጭበርብሯል ተብሎ ተሰርዞ የነበረው የ25,791 ቤቶች ዕጣ በድጋሚ ወጥቷል ለጋራ...

ጎህ ቤቶች ባንክ ወደ ቤት ልማት ለመግባት ብሔራዊ ባንክን ፈቃድ ጠየቀ

በስምንት ወራት ውስጥ 7.9 ሚሊዮን ብር ማትረፉን አስታውቋል ኢትዮጵያ ውስጥ...

የአዲስ አበባን የውኃ ችግር ለመቅረፍ የከርሰ ምድር ውኃ የያዘ መሬት ማግኘት አልተቻለም ተባለ

በአዲስ አበባ ከሦስት እጥፍ በላይ የውኃ ታሪፍ መጨመሩ ተጠቆመ በቀን...
- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

ተወግዘው የነበሩ ሦስቱ ሊቀጳጳሳትና 20 ተሿሚ ኤጲስ ቆጶሳት ውግዘት ተነሳ

_ቀሪዎቹ ሦስት ህገወጥ ተሿሚዎች የመጨረሻ እድል ተሰጥቷቸዋል ​ ጥር 14...

በሕወሓት አመራሮች ላይ ተመስርቶና በሂደት ላይ የነበረው የወንጀል ክስ ተቋረጠ

በቀድሞ የትግራይ ክልል ፕሬዚደንት ደብረጽዮን ገብረሚካኤ,(ዶ/ር)ና ባለፈው ሳምንት በተሾሙት...

[የምክር ቤቱ አባል ላቀረቡት ጥያቄ በተሰጣቸው ምላሽ አቤቱታቸውን ለክቡር ሚኒስትሩ እያቀረቡ ነው]

ክቡር ሚኒስትር እየሆነ ያለው ነገር ትክክል ነው? ምነው? ምክር ቤቱም ሆነ...

የጉራጌ የክልልነት ጥያቄ ትኩሳት

ቅዳሜ መጋቢት 16 ቀን 2015 ዓ.ም. በጉራጌ ዞን ወልቂጤ...

አይ የእኛ ነገር!

የዛሬው ጉዞ ከጀሞ ወደ ፒያሳ ነው፡፡ መንገዱ ለሥራ በሚጣደፉ፣...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[የምክር ቤቱ አባል ላቀረቡት ጥያቄ በተሰጣቸው ምላሽ አቤቱታቸውን ለክቡር ሚኒስትሩ እያቀረቡ ነው]

ክቡር ሚኒስትር እየሆነ ያለው ነገር ትክክል ነው? ምነው? ምክር ቤቱም ሆነ አባላቱ የተከበሩ ተብለው የሚጠሩት በምክንያት አይደለም እንዴ? ትክክል ነው። ምክንያቱም፣ ምክር ቤቱ ትልቁ የሥልጣን አካል ነው፣...

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሚያከብሯቸው አንድ የቀድሞ ጉምቱ ፖለቲከኛ ስልክ ተደውሎላቸው እያወሩ ነው]

አንዳንድ ነገሮች ቢያሳስቡኝ ነው ቀጠሮ ሳልይዝ ላወራህ የፈለኩት ክቡር ሚኒስትር? እርሶዎማ ቀጠሮ መያዝ አያስፈልግዎትም። ምን ገጠመዎት? እኔማ ምን ይገጥመኛል፣ አንተኑ ልጠይቅህ እንጂ? ምን? እውነት ለመናገር የማየው ነገር አሳስቦኛል። ይንገሩኝ...

[የባለሥልጣኑ ኃላፊ የቴሌኮም ኩባንያዎች የስልክ ቀፎ የመሸጥ ፈቃድ እንዳላቸው ለማረጋገጥ ክቡር ሚኒስትሩ ጋር ደወሉ]

ክቡር ሚኒስትር ዕርምጃ ከመውሰዳችን በፊት አንድ ነገር ለማጣራት ብዬ ነው የደወልኩት። እሺ ምንን በተመለከተ ነው? የቴሌኮም ኩባንያዎችን በተመለከተ ነው። የቴሌኮም ኩባንያዎች ምን? የቴሌኮም ኩባንያዎች የሞባይል ቀፎ እንዲሸጡ በሕግ...