- Advertisement -

የቦብ ማርሌ ሐውልት ዝውውር

ሐቻምና በምሥራቅ አዲስ አበባ ኢምፔሪያል አካባቢ ተተክሎ የነበረው የቦብ ማርሌ ሐውልት፣ በመስቀለኛ መንገድ የማስፋፋት ሥራ ሳቢያ ሰኔ 16 ቀን 2009 ዓ.ም. እንዲነሳ ተደርጓል፡፡ አራት ሜትር ቁመት ያለው ሐውልቱ ቦብ ‹‹አፍሪካ ዩናይት›› ብሎ ሲዘፍን የሚያሳይ ሲሆን፣ የተሠራውም በቀራፂ ተስፋ ብዙነህ ነው፡፡ ሐውልቱ በቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተ ክርስቲያን እና በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን አዳራሽ መካከል፣ በፊንፊኔ ወንዝ ዳርቻ በተሠራው የሕዝብ መናፈሻ መካከል ይቆማል ተብሏል፡፡ ሚያዝያ 11 ቀን 2007 ዓ.ም. በይፋ የተመረቀው የቦብ ማርሌ ሐውልት ግንባታ ሒደት አምስት ዓመት መውሰዱ፣ አደባባዩን ለመጠገን ብቻ ከ200 ሺሕ ብር መውጣቱን ድምፃዊ ዘለቀ ገሠሠን ጠቅሶ ሪፖርተር መዘገቡ ይታወሳል፡፡ ፎቶዎቹ የድሮውንና የአሁኑን የአደባባዩን እና የሐውልቱን ገጽታ ያሳያሉ፡፡

ፎቶ በታምራት ጌታቸው

አውጣኝ

…ፍቅር ከሌለው ሰላምታ

ውበት ከሌለው ፈገግታ

…ጥልቀት ከሌው እውቀት

- Advertisement -

መሠረት ከሌለው እምነት

እውነት ከሌለው ምርምር

ደግነት ከሌለው ፍቅር

አውጣኝ

ህሊናዬ አውጣኝ፡፡

እኔ በቁሜ እንዳላይ የበድን ሬሳን ዕጣ

ህሊናዬ ጠንከር በርታ ባስቀይምህ

ቢያስቀይሙህ

በቀላሉ አትረታ

ጥለኸኝ እንዳትበረግግ

ፈርጥጠህ እንዳትጠፋ፡፡

  • ፈቃደ አዘዘ (1994)

******

 

‹‹ማን ነው?…››

አንዱን  ሊቅ ‹‹ማን ነው ብልህ?›› ቢሉት፡-

  ከያንዳንዱ ሰው ሊማር የሚችል፤

‹‹ማን ነው ጠንካራ ሰው?›› ቢሉት፡-

 ስሜቱን የሚቆጣጠር፤

‹‹ማን ነው ሀብታም?›› ቢሉት፡-

  በቃኝን የሚያውቅ፤

‹‹ማን ነው የተከበረ ሰው?›› ቢሉት

  ሰውን የሚያከብር፤  ብሎ መለሰ ይባላል፡፡

  • የወግ ገበታ
  •  

አሽከርካሪ አልባ መኪናዎችን የምትፈትነው ካንጋሩ

የቮልቮ ራሱን በራሱ የሚያሽከረክር የመኪና ቴክኖሎጂ፣ መንገድ ላይ የሚያጋጥሙ ካንጋሩዎችን መለየት ባለመቻሉ ችግር ውስጥ ገብቷል፡፡

ቢቢሲ እንደዘገበው፣ የስዊድን መኪና አምራቹ 2017 ኤስ 90 እና ኤክስ ሲ 90 ሞዴሎች እንስሳትን መለየት የሚያስችል ቴክኖሎጂ አላቸው፡፡ ቴክኖሎጂውም ድብ፣ ኤልክና ካሪቡን መለየት ይችላል፡፡ ሆኖም ካንጋሩን ለመለየት መቸገሩ ተገልጿል፡፡ የአውስትራሊያ ብሔራዊ የሞተረኞች አሶሲየሽንም 80 በመቶ የሚሆነው የመኪና ግጭት ከካንጋሩ ጋር ነው ብሏል፡፡ የቮልቮ የደኅንነት ኢንጅነሮች ካንጋሩዎች በየመንገዱ ላይ ያላቸውን ባህሪ መቅረጽ የጀመሩት በ2015 ሲሆን፣ የሚገኘው መረጃም የመኪኖች ራዳር ካንጋሩዎችን እንዲለዩ ለማስቻል፣ ከዚህ ጋር የተያያዙ አደጋዎችንም ለማጥፋት መሆኑን ዘገባው ያሳያል፡፡

******

    በረሃውን ገነት የሚያደርገው ‹‹የነፍስ ምግብ››

አንድ ሊቅ ሰው ‹‹እኔ ጠንካራ ሠራተኛ ነው አዕምሮዬ ሲደነዝዝ ቴኒስ በመጫወት እደሰታለሁ ሐዘኔን ልረሳው እንድችል ያደረገኝ ግን የተዋቡ ሙዚቆችን መስማት ነው፤›› አለ በእርግጥም በሰውና በዓለሙ መካከከል ፍፁም ሰላም ሰጭ ሁኖ የሚያስታርቀው የዕርቅ መስዋዕት ጣዕም ያለው ዘፈንና ሙዚቃ ቃና ነው፡፡

ውብ ድምፅ ያላቸው ወፎች በረሃ አገራቸው ነው፡፡ ቃና ባለው ዜማ ከተዋበ ድምፃቸው ጋራ ሲዘምሩ ግን በረሃውን ገነት ያደርጉታል፡፡ እንዳዘነም ልብ የነበረውን ምድረ በዳ የገነት ያህል ሊለውጡት ችሎታ ሲኖራቸው አዳኞች አይተዋል፡፡ እንዲሁም የላባው ውበት ሊያኮራው የሚችል የቁራ አሞራ ደግሞ በዜማውና በድምፁ ክፋት እንደገነት ያማረችውን አገር በረሃ ያደርጋታል፡፡

ሰውም በሚኖርበት ርስቱ ላይ እንዲሁ ነው፡፡ የተዋጣ ቅያስ ባላቸው መንገዶች መጓዝ አይታው ሁሉ ደስ ያሰኘዋል፡፡

አበቦችም በተተከሉበት ቦታ መጠለል አዲስ ስሜትና ዕረፍት ይሰጠዋል፡፡ ቅርፁ እጅግ አምሮ በታነፀ ቤት መኖርም ይመቸዋል፡፡ በሰገነት መቀመጥም እጅግ ክብር ያለው ሆኖ ያገኘዋል፡፡ ነገር ግን የነፍሰን አሥራው በማንቀሳቀስ ሰውን ደስ ሊያሰኘው የሚችል ጣዕም ያለው ሙዚቃና ባህል ያለው ዘፈን ባይኖር የማንኛውም የሚታይ ውበት ሁሉ ግምቱ አባይ ይሆናል፡፡

ተመስገን ገብሬ ‹‹ሰንደቅ ዓላማችን›› (ኀዳር 1935)

                        *******

- Advertisement -

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን

ከ ተመሳሳይ አምዶች

የሃዋሳ ሐይቅ ዳርቻው ሩጫ

ዓመታዊው የሃዋሳ ሐይቅ ዳርቻ የግማሽ ማራቶንና በተለያየ ዕድሜ ክልል ውስጥ ያሉ የተሳተፉባቸው የሩጫ ውድድሮች ባለፈው እሑድ (የካቲት 2) ተካሂደዋል፡፡ በተለይ የ2017 ሶፊ ማልት ሃዋሳ...

‹‹አሻም አዲ››

“አሻም አዲ! አሻም አዲ! አሻም አዲ!..." አዲ የጎረቤታችን አዛውንት ሴት ነበሩ፡፡ ሳይማልድ ከሰፈራችን እራቅ ብሎ ካለ ጫካ ሰርጥ የለቀሙትን እንጨት፣ ቅጠልና ጭራሮ ተሸክመው እያመጡ...

አታልቅስ አትበሉኝ

 አታልቅስ በሉኝ  ግዴለም ከልክሉኝ፣  የፊቴን ፀዳል  አጠልሹት በከሰል ፣  የግንባሬን ቆዳ  ስፉት በመደዳ፣  ጨጓራ አስመስሉት።               ግዴለም።   አትጫወት በሉኝ   ዘፈኔን ንጠቁኝ።              ግዴለም።   ብቻ፣  አታልቅስ አትበሉኝ  አትጩህ አትበሉኝ።    ደበበ ሰይፉ ‹‹ለራስ የተጻፈ ደብዳቤ (የብርሃን...

‹‹ወይዘሪት አገው››

የአገው ፈረሰኞች 85ኛው በዓል በእንጅባራ ከተማ ባለፈው ሳምንት ሲካሄድ ከነበሩት ሁነቶች አንዱ ለሁለተኛ ጊዜ የተካሄደው የቁንጅና ውድድር ነበር፡፡ ከ11 ተወዳዳሪዎች መካከል አሸናፊ ሆና ‹‹ወይዘሪት...

መኖር መኖር መኖር!

በማይ በምሰማው አንዳንዴ ስገረም ሕይወት ከናላማው ስህተት ይሆን እንዴ፤ በሞት የሚታረም? ማለት ይቃጣኛል የዚህ ዓለም ኑሮ ጥያቄ ወርውሮ ምላሽ ያሳጣኛል፡፡ ደሞ አንዳንዴ ሳስብ ስለሰው ልጅ ሥራ የሰናፍጭ ቅንጣት በምታክል ጥበብ የሚንድ ተራራ በጨለመ ምድር፤ ብርሃን እሚዘራ በሰማይ...

መናገር እንጂ መጻፍ የማይችሉ ምሁራን

በአሁኑ ጊዜ መናገር እንጂ ከማይጽፉት ሰዎች አንዱ ስለሆኑ ታላቅ ሰው ለመጻፍ እየሞከርኩ ነው። ለመሆኑ አንዳንድ ምሁራን ለምን መናገር እንጂ መጻፍ አይችሉም? አንዳንድ ምሁራን ምንም እንኳን...

አዳዲስ ጽሁፎች

የጤናው ዘርፍ ባለፉት ስድሥት ወራት

የወባ በሽታ ከሰሃራ በታች በሚገኙ የአፍሪካ አገሮች ዋነኛ የጤናና የማኅበራዊ ቀውስ መንስዔ ነው፡፡ የዓለም ጤና ድርጅት እ.ኤ.አ. በ2024 ያወጣው መረጃም 263 ሚሊዮን ሰዎች የወባ...

የአዲስ አበባ የኮሪደር ልማት በባለሙያ ዓይን

(በጎ ጎኖችና እርምት የሚፈልጉ ጉዳዮች) በዮሐንስ መኮንን በጥር ወር 2016 ዓ.ም. የአዲስ አበባ ዋና ዋና ኮሪደሮችን በማዘመን ከተማዋን ለነዋሪዎቿና ለጎብኚዎቿ ምቹ ያደርጋታል የተባለ ፕሮጀክት በ43 ቢሊዮን...

በልዩነት ውስጥ ሆነንም እስኪ እንነጋገር

በገነት ዓለሙ ዴሞክራሲ መብቶችና ነፃነቶች የሚሠሩበት የሕዝብ አስተዳደር ነው፡፡ ሰብዓዊ መብቶችንና ነፃነቶችን መኗኗሪ ያደረገ ሥርዓት ነው፡፡ እነዚህ መሠረታዊ መብቶችና ነፃነቶች በተፈጥሮ የተገኙ፣ ሰው በመሆናችን ብቻ...

ለጤናማ የትራፊክ ፍሰትና ለመንገድ ደኅንነት ቅጣት መጣል ብቻውን መፍትሔ አይሆንም!

በአዲስ አበባ ከተማ ለተሽከርካሪዎች ምቹ የሆኑ መንገዶችን እየተመለከትን ነው፡፡ ከአዳዲሶቹ መንገዶች ባሻገር አንዳንድ ነባር መንገዶች የማስፋፊያ ሥራ ታክሎባቸው አገልግሎት ላይ ውለዋል፡፡ ከኮሪደር ልማቱ ጋር...

የግጭት አዙሪት ውስጥ ሆኖ የአፍሪካ ማዕከል መሆን ያዳግታል!

የአፍሪካ ኅብረት 38ኛው የመሪዎች ጉባዔ በአዲስ አበባ ሲካሄድ ብዙ ትዝ የሚሉ ጉዳዮች አሉ፡፡ እጅግ በጣም አሰልቺ፣ ውጣ ውረድ የበዛበትና ታላቅ ተጋድሎ ተደርጎበት ከከፍተኛ ዲፕሎማሲያዊ...

አገሬ ምንተባልሽ – ልብ ያለው ልብ ይበል

በቶማስ በቀለ ይቺ አገራችን ብዙ ተብሎላታልም፣ ብዙ ተወርቶባታልም፣ አገሪቱ በቅኝ ያልተገዛች ብቸኛ አገር (ላይቤሪያን ጨምሮ) ከመሆኗ አኳያ የሚነገርላት ብዙ ጥሩና የሚገርሙ ነገሮች ያሉትን ያህል፣ ከረሃብ...
[the_ad id="124766"]

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን