Saturday, April 1, 2023
- ማስታወቂያ -
- ማስታወቂያ -

ብርሃን ባንክ የምርት ገበያን የክፍያ ሥርዓት ተቀላቀለ

- ማስታወቂያ -

ተዛማጅ ፅሁፎች

ብርሃን ኢንተርናሽናል ባንክ በኢትዮጵያ ምርት ገበያ የሚካሄዱ ግብይቶችን በዘመናዊ የባንክ የክፍያ ሥርዓት ለማስተናገድ ከምርት ገበያው ጋር ስምምነት በመፈረም አሥራ አንደኛው ባንክ ሆነ፡፡

ብርሃን ባንክ ከምርት ገበያ ጋር ዘመናዊ የክፍያ አገልግሎትን ለመስጠት የሚያስችለውን ስምምነት ሰኔ 14 ቀን 2009 ዓ.ም. በምርት ገበያው ዋና መሥሪያ ቤት ተፈራርሟል፡፡

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ እንደገለጸው፣ ከብርሃን ኢንተርናሽናል ባንክ ጋር የተደረሰው ስምምነት የምርት ገበያውን የክፍያ ሥርዓት ለማቀላጠፍና ለማዘመን የሚያደርገውን ጥረት ለማሳካት ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል፡፡ ይህም ብቻ ሳይሆን፣ የግብይት ፈጻሚዎችም ተጨማሪ የክፍያ ባንክ እንዲኖራቸው ዕድል ይሰጣል ብሏል፡፡

ብርሃን ባንክን ጨምሮ እስካሁን ከ11 ባንኮች ጋር ተመሳሳይ ስምምነቶችን በማድረግ ተገበያዮች ግብይት በፈጸሙ ማግሥት አቅራቢዎችና ሻጮች የተገበያዩበትን ገንዘብ በቀጥታ ገዥውን ከፈጸመው የባንክ ሒሳብ፣ ሽያጩን ወደ ፈጸመው የባንክ ሒሳብ እንዲዛወር በማድረግ አገልግሎት የሚሰጥበት አሠራር ነው፡፡ ከምርት ገበያው ጋር እንዲህ ዓይነቱን አገልግሎት ከስምንት ዓመታት በፊት በመፈረም ቀዳሚው ዳሽን ባንክ ነው፡፡

ባለፉት አሥር ዓመታት ውስጥ ከምርት ገበያው ጋር ስምምነት የፈጸሙት ባንኮች በዓመት በቢሊዮን የሚቆጠረውንና በግብይቶች አማካይነት የሚመነጨውን ገንዘብ ከገዥ ወደ ሻጭ የባንክ ሒሳብ እንዲዘዋወር በማድረግ ሲሠሩ  ቆይተዋል፡፡ ምርት ገበያው በበጀት ዓመቱ ግማሽ ዓመት ብቻ ከአሥር ቢሊዮን ብር በላይ ግብይቶችን አስፈጽሟል፡፡

እንዲህ ያለው በባንኮች ላይ የተመሠረተ የክፍያ ሥርዓት ገበያውን በመተማመን ላይ የተመሠረተ እንዲሆን እንደሚያደርገው የሚገልጸው የምርት ገበያው መረጃ ለዘመናዊ የክፍያ አገልግሎቶች መጎልበት የራሱ ድርሻ ይኖረዋል ተብሏል፡፡

ሐሙስ፣ ሰኔ 13 ቀን 2009 ዓ.ም. በብርሃን ባንክና በኢትዮጵያ ምርት ገበያ መካከል የተደረገውን ስምምነት የፈረሙት የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ዋና አስፈጻሚ አቶ ኤርሚያስ እሸቱና የብርሃን ኢንተርናሽናል ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አብርሃም አላሮ ናቸው፡፡ 

spot_img
- Advertisement -spot_img

የ ጋዜጠኛው ሌሎች ፅሁፎች

- ማስታወቂያ -

በብዛት ከተነበቡ ፅሁፎች