Friday, March 24, 2023
- ማስታወቂያ -
- ማስታወቂያ -

በዱከም የነዳጅ ማጠራቀሚያ ዴፖ ሊገነባ ነው

- ማስታወቂያ -

ተዛማጅ ፅሁፎች

  • ዘንድሮ ለ3.4 ሚሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ነዳጅ ሁለት ቢሊዮን ዶላር ወጪ ተደርጓል

የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ኢንተርፕራይዝ ከአዋሽ በመቀጠል በአዲስ አበባ ዙሪያ ኦሮሚያ ልዩ ዞን ዱከም አካባቢ የነዳጅ ማጠራቀሚያ ዴፖ ሊገነባ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ኢንተርፕራይዝ ዋና ዳይሬክተር አቶ ታደሰ ኃይለ ማርያም ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ኢንተርፕራይዙ የነዳጅ ዴፖ ግንባታ ለማካሄድ ከኦሮሚያ ክልል አሥር ሔክታር መሬት ተረክቧል፡፡

በአዋሽ አካባቢ ቀደም ሲል 100 ሺሕ ኪዩቢክ ሜትር መጠባበቂያ ነዳጅ የሚይዙ ዴፖዎች እንዳሉ ዋና ዳይሬክተሩ ገልጸው፣ በዚሁ ቅጥር ግቢ ውስጥ ለዕለት ተዕለት ተግባር የሚውል 36 ሺሕ ኪዩቢክ ሜትር የሚይዝ የነዳጅ ማጠራቀሚያ ዴፖ ግንባታ  እየተካሄደ ነው ብለዋል፡፡ ‹‹የአዋሽ ፕሮጀክት በአጠቃላይ ግንባታው ከ90 በመቶ በላይ ሆኗል፡፡ በቀጥታ ከባቡር ነዳጅ መቀበል የሚችልበት ደረጃ ላይ ደርሷል፤›› ሲሉ አቶ ታደሰ ግንባታው ያለበትን ደረጃ ጠቁመዋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪ የዴፖ ግንባታ በጥልቀት እንደሚካሄድ አቶ ታደሰ ገልጸው፣ በዱከም የነዳጅ ማጠራቀሚያ ዴፖ ለመገንባት ፕሮጀክት መዘጋጀቱን አመልክተዋል፡፡

በሚቀጥለው ዓመት በዱከም ሊገነባ ለታቀደው ዴፖ የዲዛይንና የአዋጭነት ጥናት እንደሚካሄድና ይህም ከተጠናቀቀ በኋላ ወደ ግንባታ እንደሚገባ አክለዋል፡፡

ባቡሩ ሙሉ ለሙሉ ሥራ ሲጀምር አገሪቱ የምታስገባውን 60 በመቶ ያህል ነዳጅ እንደሚያጓጉዝ የተናገሩት አቶ ታደሰ፣ በ2009 ዓ.ም በአጠቃላይ 3.4 ሚሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ነዳጅ ወደ አገር እንደገባና እንደሚገባ፣ ለነዳጅ ግዥና ለተያያዥ ክንውኖች ሁለት ቢሊዮን ዶላር ወጪ እንደተደረገ አቶ ታደሰ አመልክተዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት በተለይ የባቡር መስመሩ ግንባታ ከተገባደደ በኋላ ዘግይቶም ቢሆን ከሆራይዘን ወደብ ጋር የባቡር መስመሩን ለማገናኘት የሚያስችል ግንባታ እየተጀመረ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

ነዳጅ በባቡር ማመላለስ አዋጭ ቢሆንም፣ ከአዲስ አበባ (ሰበታ) እስከ ጅቡቲ ድረስ ያለው 756 ኪሎ ሜትር የባቡር መስመር በሚገነባበት ወቅት፣ የነዳጅ ማጠራቀሚያ ዴፖ ግንባታ ቀደም ብሎ አለመታሰብን የሚያመላክቱ አሉ፡፡

ከእነዚህ መካከል የባቡር መስመሩ ግንባታ ሲካሄድ የነዳጅ ማጠራቀሚያ ዴፖና አብዛኛውን የኢትዮጵያ ነዳጅ የሚገባበትን የጂቡቲ ሆራይዘን ወደብ ከባቡር ሐዲዱ ጋር እንዲገናኝ አለመደረጉ ነው፡፡

አንድ የባቡር ዋገን (ሞተር) 36 ፉርጎዎችን የመጎተቱ አቅም እንዳለው አቶ ታደሰ ገልጸው፣ አንድ ዋገን 70 ከባድ ተሽከርካሪዎች የሚይዙትን ያህል ነዳጅ የማጓጓዝ አቅም አለው ብለዋል፡፡ ‹‹አንድ ፉርጎ 80 ሺሕ ሊትር ሲይዝ፣ አንድ ከባድ ተሽከርካሪ ግን 45 ሺህ ሊትር ይይዛል፤›› በማለት የባቡርን አዋጭነት ጠቁመዋል፡፡

spot_img
- Advertisement -spot_img

የ ጋዜጠኛው ሌሎች ፅሁፎች

- ማስታወቂያ -

በብዛት ከተነበቡ ፅሁፎች