Friday, June 9, 2023
- ማስታወቂያ -
- ማስታወቂያ -

የአማራ ብድርና ቁጠባ ተቋም በአፍሪካ የባንኮች ሽልማት በፋይናንስ ተደራሽነት ዘርፍ ለሽልማት ታጨ

- ማስታወቂያ -

ተዛማጅ ፅሁፎች

የአገሪቱ የግልም ሆነ የመንግሥት ባንኮች ለውድድሩ ዕጩ መሆን ባልቻሉበት የዓመቱ የአፍሪካ ባንኮች ሽልማት መስክ፣ የአማራ ብድርና ቁጠባ ተቋም፣ በፋይናንስ መስክ ዕጩ መሆኑ ታወቀ፡፡

‹‹አፍሪካ ባንከር ሜጋዚን›› የሚባለውና አይሲ ግሩፕ በተባለው የእንግሊዝ ኩባንያ የሚታተመው መጽሔት፣ በየዓመቱ በሚያካሂደው የፋይናንስ ዘርፉ ላይ ያተኮረ ውድድር ዘንድሮ በአሥር ምድቦች በሚካሄደው ሽልማት፣ በፋይናንስ ተደራሽነት ዘርፍ ለሽልማት የታጨው የአማራ ብድርና ቁጠባ ተቋም፣ ከዚህ ቀደምም የዓመቱ ምርጥ የብድርና ቀጠባ ተቋም ተብሎ መሸለሙን ለማወቅ ተችሏል፡፡

በአገሪቱ ከሚገኙ ከ35 የማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት መካከል ከቀደምቶቹ አንዱ የሆነው የአማራ ብድርና ቁጠባ ተቋም፣ እስከ ካቻምና ድረስ ከ500 በላይ ቅርንጫፎችን በመክፈት በመላው አማራ ክልል የፋይናንስ ተደራሽነትን ለማስፋፋት መንቀሳቀሱ ለሽልማት እንዲታጭ ካበቁት መካከል ይጠቀሳል፡፡

አነስተኛ ገንዘብ አቅራቢው የአማራ ብድርና ቁጠባ ተቋም፣ ዘንድሮ በድጋሚ ለዕጩነት የቀረበው በፋይናንስ ተደራሽነት መስክ ይሁን እንጂ ከጥቂት ዓመታት ቀደም ብሎም የዓመቱ የአነስተኛ ገንዘብ አቅራቢ ሽልማትን ከመቀዳጀት ባሻገር፣ የግራሚን ሽልማትም ያገኘበት ጊዜ እንደነበር ከተቋሙ የተገኘው መረጃ ይጠቁማል፡፡ ይህ ሽልማት የማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት መሥራቹ ባንግዳሌሻዊ ዩኑስ መሐመድ (ዶ/ር) አማካይነት ለዓለም በተዋወቀው የግራሚን ባንክ ፋውንዴሽን መታሰቢያነት የሚሰጥ ሽልማት ነው፡፡ ከዚህም ባሻገር ምርጥ ተቋም እንዲሁም ምርጥ የተቋም መሪ የሚሉ ሽልቶችን ከኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ እ.ኤ.አ. በ2012 ማግኘቱም ተጠቅሷል፡፡

በዘንድሮው የአፍሪካ ባንከር መጽሔት የሽልማት ዘርፎች ውስጥ በዕጩነት የተካተተው አማራ ብድርና ቁጠባ ተቋም በታጨበት የፋይናንስ ተደራሽነት ሽልማት ዘርፍ ማሸነፍ ከቻለ፣ ግንቦት 15 ቀን 2009 ዓ.ም. በህንድ አህመዳባድ ከተማ በሚካሄደው የሽልማት ሥነ ሥርዓት ላይ ታዳሚ እንደሚሆን አይሲ ፐብሊኬሽንስ ያውጣው መርሐ ግብር ይጠቁማል፡፡ በዚህ ሥነ ሥርዓት በአፍሪካ ልማት ባንክ ዕውቅና ተሰጥቶት የሚከናወን ሲሆን፣ ሌሎችም በአፍሪካ የሚንቀሳቀሱ የግልና የመንግሥታቱ ባንኮች ድጋፍ የሚሰጡት ሥነ ሥርዓት እንደሆነ ሽልማቱን ያሰናዳው ተቋም ለሪፖርተር ከላከው መግለጫ ለመረዳት ተችሏል፡፡

 

 

 

spot_img
- Advertisement -spot_img

የ ጋዜጠኛው ሌሎች ፅሁፎች

- ማስታወቂያ -

በብዛት ከተነበቡ ፅሁፎች