Friday, December 8, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊከ4.7 ሚሊዮን ብር በላይ የውጭ ምንዛሪ አሳጥተዋል የተባሉ ቡና ነጋዴዎች ተከሰሱ

ከ4.7 ሚሊዮን ብር በላይ የውጭ ምንዛሪ አሳጥተዋል የተባሉ ቡና ነጋዴዎች ተከሰሱ

ቀን:

     በሐሰተኛ የቀበሌ መታወቂያ የቡና ላኪነት የንግድ ፈቃድ በማውጣትና ሐሰተኛ የውክልና ሰነዶችን በመጠቀም የብቃት ማረጋገጫ በመውሰድ፣ 223,846 ዶላር ወይም 4,702,506 ብር የውጭ ምንዛሪ አሳጥተዋል የተባሉ ሦስት ግለሰቦች ክስ ተመሠረተባቸው፡፡

የፌዴራል ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ የመሠረተው ክስ እንደሚያስረዳው ድርጊቱን በመመሳጠር የፈጸሙት አቶ አብዱልዋሀድ ሞሐመድ፣ ወ/ሮ ሉባባ ከሊልና አቶ ሸሪፍ ሱሌማን ናቸው፡፡

ተከሳሾቹ በመመሳጠር ጉዳይ አስፈጻሚ ነው በተባለ ቴዎድሮስ ከበደ ስም ሐሰተኛ መታወቂያ በማውጣትና ሐሰተኛ የውክልና ሰነድ በማስያዝ፣ ከግብርና ሚኒስቴር የቡና ላኪነት ብቃት ማረጋገጫና ከንግድ ሚኒስቴር ንግድ ፈቃድ እንዲያወጣ ማድረጋቸውን ክሱ ይገልጻል፡፡ ለዚህ አገልግሎቱም 300 ሺሕ ብር እንደተከፈለው ተገልጿል፡፡

 በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በአብዱልዋሀድ ሞሐመድ ስም 200,000 ብር ገቢ በማድረግና ከግብርና ሚኒስቴር ገንዘብ በባንክ መኖሩን የሚገልጽ ደብዳቤ በማጻፍ፣ ቡናን ኤክስፖርት ለማድረግ የሚያስችል በቂ አቅም እንዳላቸው በማስመሰል፣ የተሳሳተ ግምት እንዲያዝ ማድረጋቸውንም ዓቃቤ ሕግ በክሱ አብራርቷል፡፡

በአንደኛ ተከሳሽ አቶ አብዱልዋሀድ ስም በኦሮሚያ ኢንተርናሽናል ባንክና በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተደጋጋሚ ገንዘብ በማስገባት፣ ከኢትዮጵያ ምርት ገበያ 694.7 ቶን ቡና ገዝተው ሳይልኩ መቅረታቸውንም አክሏል፡፡ በመሆኑም ሁሉም ተከሳሾች ከባድ የማታለል ወንጀል በመፈጸማቸው ክስ እንደተመሠረተባቸው ዓቃቤ ሕግ በክሱ አስረድቷል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ታዋቂው የኤሌክትሮኒክስ ብራንድ አይቴል የስትራቴጂ ለውጥ አካል የሆነውን አዲስ አርማ እና መለዮ ይፋ አደረገ።

በአለማችን ታዋቂ ከሆኑት የኤሌክትሮኒክስ ብራንዶች መካከል አንዱ የሆነው እና...

የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ጥሪ ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ

ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ የሸገር አነስተኛ የፋይናንስ...

[የክቡር ሚኒስትሩ ጸሐፊ፣ የሌላ ሚኒስትር ጸሐፊ ከሆነችው የቅርብ ወዳጇ ጋር በስልክ እየተጨዋወቱ ነው]

አንቺ ግን ምን ሆነሽ ነው? ጠፋሁ አይደል? ጠፋሁ ብቻ?! ምን ላድርግ ብለሽ...

በሱዳን ላይ ያጠላው የመከፋፈል ዕጣና ቀጣናዊ ተፅዕኖው

የሱዳን ጦርነት ስምንተኛ ወሩን እያገባደደ ይገኛል፡፡ ጄኔራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን...