Friday, December 8, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናየተንዳሆ ስኳር ፋብሪካ ሰባት ኃላፊዎችና አንድ ባለሀብት ተከሰሱ

የተንዳሆ ስኳር ፋብሪካ ሰባት ኃላፊዎችና አንድ ባለሀብት ተከሰሱ

ቀን:

የተሰጣቸውን ኃላፊነት ያላግባብ በመገልገልና ከሥልጣቸው በላይ በመጠቀም ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ በመንግሥትና ሕዝብ ሀብት ላይ ጉዳት አድርሰዋል የተባሉ፣ በኢትዮጵያ ስኳር ኮርፖሬሽን የተንዳሆ ስኳር ፋብሪካ በተለያዩ የሥራ ኃላፊነት ላይ የነበሩ ሰባት ኃላፊዎችና አንድ ባለሀብት ላይ ክስ ተመሠረተ፡፡

የፌዴራል ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ መስከረም 12 ቀን 2010 ዓ.ም. በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ተረኛ ችሎት ክስ የመሠረተባቸው፣ በስኳር ኮርፖሬሽን የአገዳ ተከላና ፋብሪካ ግንባታ ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ አበበ ተስፋዬ (ኢንጂነር) ናቸው፡፡ እንዲሁም የመስኖና ቤቶች ግንባታ ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር  አቶ ኪሮስ ደስታ (ኢንጂነር)፣ የአገዳ ተክል ልማትና ፋብሪካ ፕሮጀክቶች ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ደረጀ ጉተማ (በሌሉበት)፣ ዋና ሥራ አስኪያጅ የነበሩት አቶ ዮሴፍ በጋሻው፣ ጊዜያዊ ዋና ሥራ አስኪያጅ የነበሩት አቶ አታክልቲ ተስፋዬ፣ የተንዳሆ ስኳር ፋብሪካ ዋና ሥራ አስኪያጅ የነበሩት ኮሎኔል መላኩ ድጋፌና ባለሀብቱ የማነ ግርማይ ጠቅላላ ተቋራጭ ሥራ ዋና አስኪያጅና ባለቤት አቶ ግርማይ የማነ በክሱ ተካተዋል፡፡

ተከሳሾቹ የተሰጣቸውን ኃላፊነት ወደ ጎን በመተውና በጥቅም በመተሳሰር የፋብሪካውን ንብረት ለሦስተኛ ወገን በትውስት ለመስጠት የሚፈቀድ አሠራር ሳይኖር፣ ለየማነ ግርማይ ጠቅላላ ተቋራጭ 40,000 ሜትር ኪዩብ ጠጠር እንዲሰጣቸው ማድረጋቸውን ዓቃቤ ሕግ በክሱ ገልጿል፡፡ ኃላፊዎቹ በቃልና በጽሑፍ በሰጡት ትዕዛዝ 24,179.66 ሜትር ኪዩብ የሚሆን የአርማታ ጠጠርም እንዲሰጥ ማድረጋቸውንም አክሏል፡፡

ኃላፊዎቹ ሲምፕሌክስ ኢንፍራስትራክቸርስ ሊሚትድ ለሚባል ድርጅትም፣ 8,955 ሜትር ኪዩብ የአርማታ ጠጠር እንዲሰጠው ማድረጋቸውንም ዓቃቤ ሕግ በክሱ ጠቁሟል፡፡ 184,654.12 ኪሎ ግራም ጠጠር በተጨማሪ ለየማነ ግርማይ ጠቅላላ ተቋራጭ በብድር በመስጠት በድምሩ በሁለቱ ድርጅቶች 25,167,676 ብር ጉዳት እንዲደረስ ማድረጋቸውን ዓቃቤ ሕግ በክሱ ገልጿል፡፡

ኃላፊዎቹ በተለያዩ ጊዜያት ኦአይኤና ሲሚፕሌክስ ኢንፍራንስትራክቸርስ ሊሚትድን ጨምሮ የአርማታ ጠጠርና ብረት ያላግባብ ለሦስቱ ድርጅቶች በመስጠት ሳያስመልሱ በመቅረታቸው፣ በፋብሪካው ላይ ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ የሚደርስ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሳቸውን ዓቃቤ ሕግ ክሱን በዝርዝር አቅርቧል፡፡

በተከሳሾች ላይ የተጠቀሰባቸው የሕግ አንቀጽ ዋስትና የሚከለክል መሆኑን በመግለጽ በማረሚያ ቤት ሆነው እንዲከራከሩ ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ሰጥቶ፣ በክሱ ላይ መቃወሚያ ካላቸው ለመጠባበቅ ለጥቅምት 8 ቀን 2010 ዓ.ም. ቀጥሮአቸዋል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ታዋቂው የኤሌክትሮኒክስ ብራንድ አይቴል የስትራቴጂ ለውጥ አካል የሆነውን አዲስ አርማ እና መለዮ ይፋ አደረገ።

በአለማችን ታዋቂ ከሆኑት የኤሌክትሮኒክስ ብራንዶች መካከል አንዱ የሆነው እና...

የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ጥሪ ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ

ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ የሸገር አነስተኛ የፋይናንስ...

[የክቡር ሚኒስትሩ ጸሐፊ፣ የሌላ ሚኒስትር ጸሐፊ ከሆነችው የቅርብ ወዳጇ ጋር በስልክ እየተጨዋወቱ ነው]

አንቺ ግን ምን ሆነሽ ነው? ጠፋሁ አይደል? ጠፋሁ ብቻ?! ምን ላድርግ ብለሽ...

በሱዳን ላይ ያጠላው የመከፋፈል ዕጣና ቀጣናዊ ተፅዕኖው

የሱዳን ጦርነት ስምንተኛ ወሩን እያገባደደ ይገኛል፡፡ ጄኔራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን...