- Advertisement -

የመንገዶች ባለሥልጣን ከፍተኛ ኃላፊዎች ከ900 ሚሊዮን ብር በላይ ጉዳት በማድረስ ተከሰሱ

  • አንድ ተጠርጣሪ በ20 ሺሕ ብር ዋስ ሲለቀቁ ሦስት ተጠርጣሪዎች  ተቀጥረዋል

በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው የታሰሩት የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን ከፍተኛ ኃላፊዎች ሥልጣናቸውን ያላግባብ በመጠቀምና በመመሳጠር ጥቅም ለማግኘትና ለማስገኘት አስበው፣ ለመንገድ ግንባታዎችና ጥራቱን ላልጠበቀ የአስፋልት ግዥ ከ900 ሚሊዮን ብር በላይ ክፍያ በመፈጸም በመንግሥትና ሕዝብ ላይ ጉዳት ማድረሳቸውን፣ የፌዴራል ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ሐሙስ መስከረም 18 ቀን 2010 ዓ.ም. በመሠረተባቸው ሁለት ክሶች አስታወቀ፡፡

ዓቃቤ ሕግ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ተረኛ ችሎት ክስ የመሠረተባቸው የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር በነበሩት አቶ ዛይድ ወልደ ገብርኤል፣ የምህንድስና ኦፕሬሽን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ አብዶ መሐመድ፣ የዕቅድና አይሲቲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር በነበሩት አቶ በቀለ ንጉሤ፣ የሰው ሀብትና የፋይናንስ አስተዳደር ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ገለሶ ቦሬ፣ ከሐረር-ጅግጅጋ መንገድ ሥራ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ሚስተር ያንግ ሬንኋ (በሌሉበት)፣ ሚስተር ኬን ሮበርትስ (በሌሉበት)፣ በግል ሥራ የተሰማሩት አቶ ከበደ ወርቅነህና አቶ እስክንድር ሰይድ (የ80 ዓመት ጡረተኛ ናቸው)፣ የባሥልጣኑ ሠራተኛ የነበሩት አቶ አማረ አሰፋ (በሌሉበት)፣ አቶ ደረጀ ኪዳኔ (በሌሉበት) እና የኢንጂነሪንግና ሬጉላቶሪ ዋና መምርያ ምክትል ዋና ዳይሬክተር የነበሩት አቶ ዘርፉ ተሰማ በአንድ የክስ መዝገብ የተጠቀሱ ናቸው፡፡

በሌላ የክስ መዝገብ ጥራት የሌለው አስፋልት ከኖክ ኢትዮጵያ ግዥ ፈጽመዋል በማለት ዓቃቤ ሕግ ክስ የመሠረተባቸው ተከሳሾች አቶ ዛይድ ወልደ ገብርኤል፣ አቶ ገብረ አናንያ ፃድቅ፣ አቶ አሰፋ ባራኪና አቶ ዘለዓለም አድማሱ ናቸው፡፡

ዓቃቤ ሕግ በመጀመርያ የክስ መዝገቡ ያካተታቸው የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን ከፍተኛ ኃላፊዎች ከሐረር-ጅግጅጋ ለሚገነባው መንገድ አማካሪነት ውል ከወሰዱት ‹‹Rougten International›› እና ‹‹Pan Africa Construction Plc›› ድርጅቶች ተቀጣሪዎችና በግል ሥራ ከተሰማሩት ሚስተር ያንግ ሬንኋ ጋር በጥቅም በመመሳጠር፣ መከፈል ከሌለበት በላይ 58,493,354 ብር ክፍያ በመፈጸም በመንግሥትና በሕዝብ ሀብት ላይ ጉዳት ማድረሳቸውን፣ ፍርድ ቤቱ ክሱን ለተከሳሾችና ለችሎት ታዳሚዎች በንባብ አሰምቷል፡፡

ዓቃቤ ሕግ በክሱ እንዳብራራው ከሐረር-ጅግጅጋ የመንገድ ግንባታና መሬት ቁፋሮ በውሉ መሠረት 20,192,409 ብር የተመደበ ቢሆንም፣ በተደረገ የለውጥ ክለሳ ወደ 26,013534 ብር ከፍ ተደርጓል፡፡ ለተቋራጩ በተፈጸሙ ተከታታይ ክፍያዎች ላይ 32,111,731 ብር  ተጨምሮ በድምሩ 58,125,266 ብር ክፍያ እንደተፈጸመለትም ክሱ ይገልጻል፡፡ ነገር ግን ክፍያው ያላግባብ እንደተከፈለ በፌዴራል ዋና ኦዲተር የክዋኔ ኦዲት በመረጋገጡ፣ ከቀጣይ ክፍያ እንዲቀነስ ወይም በሌላ መንገድ ግንባታ ላይ እንዲመለስ እንዲያደርጉ ለባለሥልጣኑ ከፍተኛ ኃላፊዎች በደብዳቤ ያሳወቃቸው መሆኑንም ዓቃቤ ሕግ በክሱ ጠቅሷል፡፡ ነገር ግን ኃላፊዎቹ ገንዘቡን ለማስመለስ ጥረት ከማድረግ ባለፈ ለመንገድ ሥራው 58,493,354 ብር የተመደበለት በማስመሰል ክፍያው እንዳይመለስ ማድረጋቸውን ዓቃቤ ሕግ በክሱ ገልጿል፡፡

ኃላፊዎቹ ከሐረር-ጅግጅጋ የመንገድ ግንባታና ፕሮጀክት በአማካሪ መሐንዲስ የቀረበው የዲዛይን የጥራት ደረጃ የአካባቢውን የኃይድሮሎጂና የሚቲዮሮሎጂ ጥናት ደረጃውን የጠበቀ መሆኑንና አለመሆኑን በመመልከት አረጋግጠው የማፅደቅ ኃላፊነት የነበረባቸው ቢሆንም፣ አለማድረጋቸው ጉልህ የሆኑ ከጅግጅጋ ከተማ ማስተር ፕላን ጋር የማጣጣምና የብረት መከላከያ ድልድዮችን የማካተት ሥራዎች ሳይከናወኑ ውል መፈጸማቸውንም አክሏል፡፡ ሁናን ሁንዳ የመንገድና ድልድይ ሥራ ኮርፖሬሽን ሥራ አስኪያጅ ሚስተር ያንግ ሬንኋ (በሌሉበት) ጋር የ346,262,115 ብር ኮንትራት ውል መፈጸማቸውን ዓቃቤ ሕግ በክሱ አብራርቷል፡፡ ሌሎች ተቋራጮችን በማግለል ወደ ትግበራ ሥራ ካስገቡ በኋላ የባለሥልጣኑ ኃላፊዎች በተደጋጋሚ የለውጥ ሥራ ትዕዛዝ (Variation Order) በመስጠት፣ የግዥ መመርያው ከሚያዘው የገንዘብ መጠን ከ30 በመቶ መብለጥ ያልነበረበት ቢሆንም፣ 31.57 በመቶ በማስበለጥ 109,329,357 ብር ጭማሪ ከሕግ ውጪ በቀጥታ ለተቋራጩ እንዲከፈል ማድረጋቸውም ተጠቁሟል፡፡ ተቋራጩም በተደጋጋሚ የሚያቀርበውን የማጠናቀቂያ ጊዜ ጭማሪ በመፍቀድ ከማጠናቀቂያ ጊዜ በላይ 1,116 የሥራ ቀናትን በመጨመር የዋጋ ማስተካከያ ብቻ 206,115,365 ብር እንዲከፈል ማድረጋቸውንም ዓቃቤ ሕግ በክሱ ገልጿል፡፡ በአጠቃላይ ከሐረር-ጅግጅጋ መንገድ ሥራ ፕሮጀክት በድምሩ 720,292,717 ብር ያላግባብ ክፍያ እንዲፈጸም በማድረግ የባለሥልጣኑ ኃላፊዎች በመንግሥትና በሕዝብ ሀብት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሳቸውን ዓቃቤ ሕግ በክሱ ገልጿል፡፡

- Advertisement -

የባለሥልጣኑ ኃላፊዎች ሌላው ጉዳት አድርሰዋል በማለት ክስ ያቀረበባቸው ከጎሬ- ጋምቤላ ከሚገነባው መንገድ ፕሮጀክት ጋር በተያያዘ ነው፡፡ ኃላፊዎቹ የመንገድ ፕሮጀክቱ ከመጀመሩ በፊት ወይም ከኮንትራክተሩ ጋር ውል ከመፈጸማቸው አስቀድሞ መብታቸው የሚነካ የአካባቢው ነዋሪዎችን ከሚመለከተው የመንግሥት አካል ጋር በመነጋገር በሕጋዊ አግባብ ማስለቀቅና ተገቢውን ዝግጅት ማድረግ ሲገባቸው፣ አለማድረጋቸውን ክሱ ይጠቁማል፡፡ ለተቋራጩም ካምፕና የኳሪ ማውጫ ቦታዎችን ሳያዘጋጁ ከኮንሶሊዴት ኮንስትራክሽን ኩባንያ ጋር ውል የተፈጸመ ቢሆንም፣ ነዋሪዎቹ ባለመልቀቃቸው 16.4 ወራት ያለ ሥራ በመቆየቱ ተቋራጩ በውሉ መሠረት ላልሠራበት ጊዜ 64,492,807 ብር ካሳ እንዲከፈለው በማድረጋቸው፣ ኃላፊዎቹ በመንግሥት ላይ ጉዳት ማድረሳቸውን ዓቃቤ ሕግ በክሱ አስታውቋል፡፡

ዓቃቤ ሕግ በሁለተኛው የክስ መዝገብ ያካተታቸው አቶ ዛይድ፣ አቶ ገብረ አናንያ፣ አቶ አሰፋና አቶ ዘለዓለም ደግሞ ኖክ ኢትዮጵያ ከሚባል ድርጅት ጥራት የሌለው አስፋልት እንዲገዛ በማድረግ የ62 ariation Ordertional Pan Africa Construction Plc,382,177 ብር ጉዳት ማድረሳቸውን አስረድተዋል፡፡

ኖክ ኢትዮጵያ ባለሥልጣኑ ያወጣውን የአስፋልት ግዥ ጨረታ ያሸነፈ ቢሆንም፣ ለቀረበው ውል የፈጸመበት ‹‹Mc-3000›› የተባለው የአስፋልት ዓይነት ከተቀመጠው ደረጃና ስፔስፊኬሸን ውጪ መሆኑ በላቦራቶሪ ተረጋግጦ እያለ፣ ኃላፊዎቹ አስፋልቱ ጥራት እንደሌለው ገልጸው፣ በ60 ቀናት ውስጥ እንዲመለስ ማድረግ ሲገባቸው ሥልጣናቸውን ያላግባብ በመጠቀም ጥቅም ላይ እንዲውል ማድረጋቸውን ክሱ ይገልጻል፡፡ አስፋልቱ ሥራ ላይ እንዲውል በተደረገባቸው መልካ-ሰደሬ፣ በደሌ-መቱ፣ ሻሸመኔ-አላባ፣ ሐዋሳ-ሀገረ ማርያምና ደጀን-ደብረ ማርቆስ የመንገድ ሥራ ፕሮጀክቶች የመሰንጠቅ፣ ወጣ ገባ የመሆን፣ የማበጥ፣ የመለጠጥ፣ የጎማ ቅርፅ መያዝ፣ ጉድጓድ መፍጠር፣ የመፈረካከስና የጠጠር መበታተን ብልሽት እንደደረሰባቸውም አክሏል፡፡ በአጠቃላይ ተከሳሾቹ በፈጸሙት ሥልጣንን ያላግባብ መገልገል የሙስና ወንጀል ክስ እንደመሠረተባቸውም ዓቃቤ ሕግ በክሱ ዘርዝሯል፡፡

ከእነ አቶ ዛይድ ወልደ ገብርኤል ጋር በተጠረጠሩበት የሙስና ወንጀል በታሰሩት  አቶ በቀለ ንጉሤ፣ አቶ ሳምሶን ወንድሙ፣ አቶ የኔነህ አሰፋና አቶ ካሳዬ ካቻ ላይ ዓቃቤ ሕግ ክስ አልመሠረተም፡፡ አቶ ካሳዬ ካቻ በበቂ ዋስ ቢፈቱ ተቃውሞ እንደሌለው በመግለጹ በ20,000 ብር ዋስትና እንዲፈቱ ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡ አቶ በቀለ፣ አቶ ሳምሶን የኔነህና በተጠረጠሩበት ከገቢያቸው በላይ ሀብት ማካበት ወንጀል ገና ምርመራውን አለመጨረሱን በመግለጽ ፍርድ ቤቱ የሰባት ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ እንዲፈቅድለት ጠይቋል፡፡

ተጠርጣሪዎቹ ደግሞ ባነሱት ተቃውሞ ዓቃቤ ሕግ ሕጉ የሚፈቅድለትን የ15 ቀናት የክስ መመሥረቻ ጊዜ ጠይቆ ተፈቅዶለታል፡፡ በተሰጠው ጊዜ ውስጥ ክስ መመሥረት ካልቻለ እነሱ ያጠፉት ጥፋት እንደሌለ የሚያረጋግጥ መሆኑን ስለሚያሳይ፣ በነፃ እንዲያሰናብታቸው ወይም የዋስትና መብታቸው እንዲከበርላቸው ጠይቀዋል፡፡

ዓቃቤ ሕግ የተጠርጣሪዎቹን የዋስትና መብት በመቃወም ለፍርድ ቤቱ እንደገለጸው፣ ሕጉ ክስ ለመመሠረት 15 ቀናትን ከመፍቀድ ወይም ይሰጣል ከማለቱ ውጪ የምርመራ ጊዜ ለመፍቀድ እንደማይከለክልና ለትርጉም ክፍት መሆኑን በመጠቆም፣ የጠየቀው ተጨማሪ ጊዜ እንዲፈቀድለት በድጋሚ ጠይቋል፡፡

የግራ ቀኙን ክርክር የሰማው ፍርድ ቤቱ በአዳር መስከረም 19 ቀን 2010 ዓ.ም. ብይን ለመስጠት የቀጠረ ቢሆንም፣ በሥራ መደራረብ ምክንያት እንዳልደረሰለት ገልጾ ለመስከረም 22 ቀን 2010 ዓ.ም. ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ ክስ የተመሠረተባቸው እነ አቶ ዛይድ ወልደ ገብርኤል የክስ መቃወሚያ ካላቸው ለመጠባበቅ ለጥቅም 3 ቀን 2010 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

 

 

- Advertisement -

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን

ከ ተመሳሳይ አምዶች

ሕወሓትን አጣብቂኝ ውስጥ የከተተው መመርያ

በሁለት አንጃ ተከፍሎ የእርስ በርስ የቃላት ጦርነት ውስጥ የገባው ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) ልዩነቱን ትቶ ወደቀድሞው አንድነቱ በመመለስ የሚጠበቅበትን ጠቅላላ ጉባዔ የማድረግ አልያም...

የትግራይ ክልል ተፈናቃዮች የኢትዮጵያ ሕዝብ ወደ ቀዬአችን እንድንመለስ ድምፅ ይሁነን ሲሉ ጠየቁ

ከሰኞ ጥር 5 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ ለሦስት ቀናት የተቃውሞ ሠልፍ በመቀሌ ከተማ እያካሄዱ ያሉት የትግራይ ክልል ተፈናቃዮች፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ ድምፅ እንዲሆናቸው ጠየቁ፡፡ በፕሪቶሪያ...

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በታጣቂዎችና ሚሊሻዎች መካከል በተከፈተ ተኩስ የሰዎች ሕይወት ማለፉ ተገለጸ

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በመተክል ዞን ቡለን ከተማ፣ በሸኔ ታጣቂዎችና በክልሉ ሚሊሻዎች መካከል በተከፈተ ተኩስ የሰው ሕይወት መጥፋቱ ተሰማ፡፡ የክልሉ ነዋሪዎች ‹‹የሸኔ ኃይሎች›› በማለት ወደ የጠሯቸው...

መንግሥትና ታጣቂዎች በየትኛውም ቦታና ሰዓት ለመነጋገር ዝግጁ ሲሆኑ ለማገዝ ዝግጁ መሆኗን አሜሪካ አስታወቀች

የሲቪክ ምኅዳሩ ሊጠበቅና ሚዲያዎች በነፃነት ሊሠሩ ይገባል ተብሏል ‹‹በአማራና በኦሮሚያ ክልሎች መንግሥትና ታጣቂዎች ገንቢ በሆነ መንገድ በየትኛውም ቦታና ጊዜ ሰላማዊ ንግግር ለማድረግ ዝግጁ ሲሆኑ ለማገዝ...

መንግሥት ባለፉት አምስት ዓመታት 1.5 ሚሊዮን ቤቶችን ገንብቻለሁ አለ

የንብረት ታክስ አዋጅ እምብዛም ማስተካከያ ሳይደረግበት መፅደቁ ቅሬታ ፈጥሯል መንግሥት ኢሕአዴግ መንግሥት ሆኖ አገሪቷን ሲያስተዳድር ለ14 ዓመታት (ከ1996 እስከ 2010 ዓ.ም.) በአገሪቱ ከገነባቸው ኮንዶሚኒየም የጋራ...

በነዳጅ ማደያዎች የቴሌብር ወኪሎች እንዲነሱ ትዕዛዝ ተላለፈ

በዮናታን ዮሴፍ ካለፈው ሳምንት ጀምሮ በሁሉም የነዳጅ ማደያዎች ሲሠሩ የነበሩ የቴሌብርም ሆነ የማደያ ወኪሎች እንዲነሱ ሲል የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን ለሁሉም የነዳጅ አከፋፋይ ኩባንያዎች፣ ለኢትዮ ቴሌኮምና...

አዳዲስ ጽሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ ቀኑን ሙሉ ከዋሉበት የሥራ አስፈጻሚ ስብሰባ ወደ መኖሪያ ቤታቸው ተመልሰው ከባለቤታቸው ጋር እያወጉ ነው]

የምን ስብሰባ ላይ ዋልኩ ነበር ያልከኝ? የሥራ አስፈጻሚ። የምን ሥራ አስፈጻሚ? የገዥው ሥራ አስፈጻሚ። ምን ገጥሟችሁ ነው የተሰበሰባችሁት? ለመረጠን ሕዝብ ቃል የገባናቸውን ተግባራት አፈጻጸም የምንገመግምበት የተለመደ ስብሰባ ነው። የገባችሁት ቃል...

ሕወሓትን አጣብቂኝ ውስጥ የከተተው መመርያ

በሁለት አንጃ ተከፍሎ የእርስ በርስ የቃላት ጦርነት ውስጥ የገባው ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) ልዩነቱን ትቶ ወደቀድሞው አንድነቱ በመመለስ የሚጠበቅበትን ጠቅላላ ጉባዔ የማድረግ አልያም...

ባንኮች እየፈጸሙት ያለው አቅርቦትንና ፍላጎትን ያላገናዘበ የውጭ ምንዛሪ ግዥ

የውጭ ምንዛሪ ግብይት በገበያ ዋጋ እንዲገበይ የወጣው ሕግ ተግባራዊ መሆን ከጀመረ ከሰባት ወራት በላይ አስቆጥሯል፡፡ ሕጉ ተግባራዊ በተደረገበት የመጀመርያው ቀን የአንድ ዶላር የምንዛሪ ዋጋ...

አሳረኛው ኑሮ!

የዛሬው ጉዞ ከቦሌ ወደ ፒያሳ ይሆን ዘንድ ግድ ሆኗል፡፡ ለምን? በኑሮ  ምክንያት፡፡ የታክሲ መሠለፊያው ወሬ የነዳጅ ጭማሪውን ተከትሎ ስለሚመጣው ተጨማሪ ታሪፍ ነው፡፡ ‹‹የእኛ ኑሮ...

የግለሰቦች ለመብታቸው ኃላፊነት አለመውሰድ ለአገር ያለው አደጋ

በያሬድ ኃይለመስቀል አንድ የማከብረው ኢኮኖሚስት አንድ መጽሐፍ እንዳነብ መራኝና ማንበብ ጀመርኩኝ። ይህንን መጽሐፍ ሳነበው ከዋናው ሐሳብ ወጣ ብሎ ስለ “የነፃ ተጓዦች ሀተታ” (The Free Rider...

‹‹የብድርና ቁጠባ ኅብረት ሥራ ማኅበራትን ኢኮኖሚያዊ አስተዋጽኦ ማጠናከር ያስፈልጋል›› አቶ ፍፁም አብርሃ፣ የአሚጎስ ብድርና ቁጠባ ኅብረት ሥራ ማኅበር መሥራችና ሥራ አስኪያጅ

አሚጎስ የብድርና ቁጠባ ኅብረት ሥራ ማኅበር ከተመሠረተ አሥራ ሁለት ዓመታት ሆኖታል፡፡ በእነዚህ ዓመታት 8,500 አባላትን ማፍራት ችሏል፡፡ አሚጎስ ስለተመሠረተበት ዓላማ፣ እያከናወናቸው ስለሚገኙ ተግባራት፣ የብድርና...
[the_ad id="124766"]

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን