Monday, October 2, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊየኦሮሚያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ሕንፃ በአዲስ አበባ ሊገነባ ነው

የኦሮሚያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ሕንፃ በአዲስ አበባ ሊገነባ ነው

ቀን:

የኦሮሚያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት በአዲስ አበባ ከተማ ዘመናዊ የሚዲያ ኮምፕሌክስ ሊያስገነባ ነው:: የሕንፃው መሠረት ድንጋይ ማክሰኞ ሚያዚያ 3 ቀን 2009 ዓ.ም. የኦሮሚያ ክልልና የፌዴራል መንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት በተገኙበት በይፋ ተቀምጧል:: የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባዔ አቶ አባዱላ ገመዳ፣ የኦሕዴድ ሊቀመንበርና የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ለማ መገርሳ፣ የኦሕዴድ ምክትል ሊቀመንበርና የውጭ ጉዳይ
ሚኒስትሩ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) እና የክልሉ ምክትል ፕሬዚዳንትና የሥራና ከተማ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ዓብይ አህመድ፣ የአዲስ አበባ ከንቲባ አቶ ድሪባ ኩማና ሌሎችም ተገኝተዋል:: ሕንፃው በቦሌ መንገድ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ጽሕፈት ቤት ፊት ለፊት በሚገኝ 4,882 ካሬ ሜትር ላይ የሚያርፍ ሲሆን፣ 14 ፎቆች ይኖሩታል ተብሏል:: አረንጓዴ ተክሎች በሕንፃው አናት ላይ እንደሚኖሩ የሕንፃ ንድፍ (ዲዛይን) ያመለክታል:: የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ለማ መገርሳ የሕንፃው ግንባታ ድርጅቱ የሚዲያ ተልዕኮውን በብቃት ለመፈጸም ያስችለዋል ብለው፣ በተጨማሪም በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆንም እንደሚያግዘው ገልጸዋል::
የሕንፃው ግንባታ ዋጋና የሥራ ተቋራጩ ማንነት አልተገለጸም:: ከባለሥልጣናቱ በስተጀርባ የሚታየው የሕንፃው ንድፍ (ዲዛይን) ነው:: (ፎቶ በመስፍን ሰለሞን)

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ተመድንና ዓለም አቀፋዊ ሕግን ከእነ አሜሪካ አድራጊ ፈጣሪነት እናድን!

በገነት ዓለሙ በእኔ የተማሪነት፣ የመጀመርያ ደረጃ ተማሪነት ጊዜ፣ የመዝሙር ትምህርት...

የሰላም ዕጦትና የኢኮኖሚው መንገራገጭ አንድምታ

በንጉሥ ወዳጅነው ፍራንክ ቲስትልዌይት የተባሉ አሜሪካዊ ጸሐፊ ‹‹The Great Experiment...

ድህነት የሀብት ዕጦት ሳይሆን ያለውን በአግባቡ ለመጠቀም አለመቻል ነው

በአንድነት ኃይሉ ድህነት ላይ አልተግባባንም፡፡ ብንግባባ ኖሮ ትናንትም ምክንያት ዛሬም...