Sunday, June 4, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናአቶ አባዱላ ገመዳ የሥራ መልቀቂያ ማስገባታቸውን አስመልክቶ የሰጡት ሙሉ መግለጫ

አቶ አባዱላ ገመዳ የሥራ መልቀቂያ ማስገባታቸውን አስመልክቶ የሰጡት ሙሉ መግለጫ

ቀን:

ባለፉት ሁለት ቀናት በተለይ በማህበራዊ ድረ ገጾችና በተለያዩ ሚዲያዎች የመልቀቂያ ጥያቄዬን የሚመለከቱ ዜናዎች ሲወጡ ተስተውለዋል፡፡ ይህንን በሚመለከት እስካሁን ያለውን ሁኔታ በአጭሩ መግለጽ ስላስፈለገ ነው፡፡
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ሆኜ ተመርጫለሁ፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባዔ በመሆንም እያገለገልኩና ሳገለግልም ቆይቻለሁ፡፡ አሁን በደረስኩበት ደረጃ በዚህ ኃላፊነት ለመቀጠል የማያስችሉኝ ሁኔታዎች ስላሉና ፍላ
ቱም ስለሌለኝ ለመልቀቅ ድርጅቴንና የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትን ጠይቄያለሁ፡፡

ድርጅቴና የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሁኔታውን አይተው ሕጋዊ መስመሩን ተከትሎ ጥያቄዬ ተገቢውን ምላሽ ያገኛል፡፡ ጥያቄዬ ተገቢውን ምላሽ ሲያገኝ የምክር ቤት አፈ ጉባዔነቴን ለመልቀቅ የፈለግኩባቸውን ምክንያቶች በዝርዝር አስረዳለሁ፡፡ እስከዛ ድረስ ግን እንደማንኛውም የሕዝብ ኃላፊነት የምክር ቤት ሥራዬን እቀጥላለሁ፡፡ ባጭር ጊዜም ምላሽ አግኝቼ ጥያቄዬ የተሳካ ይሆናል ብዬ አምናለሁ፡፡

ጥያቄዬ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባዔነት የመልቀቅ ቢሆንም፣ የመረጠኝን ሕዝብና ያስመረጠኝን ድርጅት ስለማከብር በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባልነቴ እቀጥላለሁ፡፡ ከዛ ውጪም ለሕዝብ ይጠቅማል በምላቸው ሥራዎች ባለኝ ጊዜ ተሰማርቼ የማገለግል ይሆናል፡፡ ይሄው እንዲታወቅና ከዚህ ውጪ ያለው ነገር ወደፊት ጥያቄዎቹ ምላሽ ሲያገኙ በዝርዝር የሚቀርቡ መሆኑን ለመግለጽ እወዳለሁ አመሰግናለሁ፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

አወዛጋቢው የሕገ መንግሥት ማሻሻያ ጉዳይ

በኢትዮጵያ የሕገ መንግሥት ማሻሻል ጉዳይ ከፍተኛ የፖለቲካ ውዝግብ የሚቀሰቀስበት...

 መፍትሔ  ያላዘለው  የጎዳና  መደብሮችን  ማፍረስ

በአበበ ፍቅር ያለፉት ስድስት ዓመታት በርካቶች በግጭቶችና በመፈናቀሎች በከፍተኛ ሁኔታ...

የተናደው ከቀደምቱ አንዱ የነበረው የአዲስ አበባ ታሪካዊ ሕንፃ

ዳግማዊ አፄ ምኒልክ በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ መናገሻ ከተማቸውን...

የአከርካሪ አጥንት ሕክምናን ከፍ ያደረገው ‘ካይሮፕራክቲክ’

በአፍሪካ ከጀርባ ሕመም ጋር በተያያዘ በርካታ ሰዎች ለከፍተኛ የአካል...