Sunday, June 4, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ኪንና ባህልየቅርስ ባለሥልጣን 100 የብራና መጻሕፍትን ተረከበ

የቅርስ ባለሥልጣን 100 የብራና መጻሕፍትን ተረከበ

ቀን:

ከኢትዮጵያ በሕገ ወጥ መንገድ ሊወጡ ሲሉ የተያዙ 100 የብራና መጻሕፍትን የቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለሥልጣን መስከረም 30 ቀን 2010 ዓ.ም. ከፌዴራል ፖሊስ ተረከበ።

ሃይማኖታዊና ታሪካዊ ይዘት ያላቸው ብራናዎቹ 2007 እስከ 2009 .ም. በሦስት ግለሰቦች እጅ የነበሩና ወደ ውጭ ሊወጡ ሲሉ በፌዴራል ፖሊስ በቁጥጥር ሥር የዋሉ ናቸው። 100ዎቹ ብራናዎቹ በፌዴራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ቡድን አስፈላጊው የማጣራት ሥራ ሲደረግባቸው ቆይተው ለሚመለከተው አካል እንዲሰጡ በፍርድ ቤት ብይን ያገኙ ናቸው፡፡

ቅርሶቹን ለቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለሥልጣን ያስረከቡት፣ የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ የልዩ ልዩ ወንጀል ምርመራ ዲቪዥን ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ሞላ አናጋው እንዳስታወቁት፣ ብራናዎቹ በተለያዩ መደብሮችና ቤቶች ውስጥ ሊያዙ የቻሉበት አጋጣሚ የተፈጠረው አንድ ቻይናዊ ከአገር ለመውጣት በሚያደርገው ሙከራ በእጁ ላይ በያዘው አምባር ከየት እንዳመጣ ፖሊስ በሚያጣራበት ወቅት ነው።

65 ብራናዎችና የዱር እንስሳት ውጤቶች የተገኙት የስጦታ ዕቃ መሸጫ መደብር ነጋዴ መሆኑን በርክከቡ ወቅት ተወስቷል። የተለያየ መጠን ያላቸው ብራናዎቹን የተረከቡት የቅርስ ምዝገባ፣ ቁጥጥርና ደረጃ ማውጣት ዳይሬክተር አቶ ደሳለኝ አበባውና የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮናስ ደስታ ሕገ ወጥ የቅርሶች ዝውውርን ለማቆም ሁሉም እንዲተባበር ጥሪ አቅርበዋል፡፡

 

የቅርስ ባለሥልጣን 100 የብራና መጻሕፍትን ተረከበ

 

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

አወዛጋቢው የሕገ መንግሥት ማሻሻያ ጉዳይ

በኢትዮጵያ የሕገ መንግሥት ማሻሻል ጉዳይ ከፍተኛ የፖለቲካ ውዝግብ የሚቀሰቀስበት...

 መፍትሔ  ያላዘለው  የጎዳና  መደብሮችን  ማፍረስ

በአበበ ፍቅር ያለፉት ስድስት ዓመታት በርካቶች በግጭቶችና በመፈናቀሎች በከፍተኛ ሁኔታ...

የተናደው ከቀደምቱ አንዱ የነበረው የአዲስ አበባ ታሪካዊ ሕንፃ

ዳግማዊ አፄ ምኒልክ በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ መናገሻ ከተማቸውን...

የአከርካሪ አጥንት ሕክምናን ከፍ ያደረገው ‘ካይሮፕራክቲክ’

በአፍሪካ ከጀርባ ሕመም ጋር በተያያዘ በርካታ ሰዎች ለከፍተኛ የአካል...