Wednesday, September 27, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊህፃናትን በበጉዲፈቻ ወደ ውጭ አገር መላክ የሚፈቅደው አንቀጽ ከኢትዮጵያ ቤተሰብ ሕግ እንዲሠረዝ...

ህፃናትን በበጉዲፈቻ ወደ ውጭ አገር መላክ የሚፈቅደው አንቀጽ ከኢትዮጵያ ቤተሰብ ሕግ እንዲሠረዝ ተወሰነ

ቀን:

የውጭ አገር ጉዲፈቻ የተፈጥሮ ቤተሰብ ፍቅርና እንክብካቤን ሙሉ በሙሉ የማይተካና ከዚህ ቀደም በጉዲፈቻ ወደ ውጭ አገራት የሄዱ ህፃናት ላይ የማንነት ቀውስ በማስከተሉ፣ ይህን አሠራር የሚፈቅደው የሕግ ድንጋጌ ከቤተሰብ ሕጉ እንዲሠረዝ መንግሥት ወሰነ።

በዚህም መሠረት የቤተሰብ ሕጉ ላይ ማሻሻያ የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ ዛሬ ለፓርላማ ቀርቦ ለዝርዝር እይታ ተመርቷል ። የውጭ ጉዲፈቻን በሚፈቅደው ሕግ አማካይነት ተጀምረው በፍርድ ቤት ሂደት ላይ የሚገኙ እንዲቀጥሉ ማሻሻያው ይፈቅዳል።

በሌላ በኩል የመንግሥት ሠራተኞች አዋጅ የተለያዩ ማሻሻያዎችን አካቶ ለፓርላማ የቀረበ ሲሆን፣ ለእናቶች ከወሊድ በኋላ ይፈቀድ የነበረው የሁለት ወር ዕረፍት ሦስት ወር እንዲሆን፣ በድምሩ እናቶች ለቅድመና ድህረ ወሊድ የአራት ወር እረፍት እንዲያገኙ በረቂቅ ሕጉ ተካቶ ቀርቧል።

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የአማራ ክልል ወቅታዊ ሁኔታ

እሑድ ጠዋት መስከረም 13 ቀን 2016 ዓ.ም. የፋኖ ታጣቂዎች...

ብሔራዊ ባንክ ለተመረጡ አልሚዎች የውጭ አካውንት እንዲከፍቱ ለመጀመሪያ ጊዜ የፈቀደበት መመርያና ዝርዝሮቹ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሪ አጠቃቀምንና ተያያዥነት ያላቸው ጉዳዮችን...

እነ ሰበብ ደርዳሪዎች!

ከሜክሲኮ ወደ ዓለም ባንክ ልንጓዝ ነው። ሾፌርና ወያላ ጎማ...