Friday, December 8, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናየፍትሕ ዋና አዘጋጅ ከዝዋይ እስር ቤት ተፈታ

የፍትሕ ዋና አዘጋጅ ከዝዋይ እስር ቤት ተፈታ

ቀን:

የፍትሕ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ የነበረው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ከሦስት ዓመታት የእስር ቤት ቆይታ በኋላ ዛሬ ጥቅምት 5 ቀን 2010 ዓ.ም. ጠዋት ከዝዋይ እስር ቤት ተፈታ፡፡    

የዛሬ ሦስት ዓመት ጥቅምት 3 ቀን 2007 ዓ.ም. የታሰረው ተመስገን የተከሰሰው ለአመጽ የሚያነሳሱ ጽሑፎችን በመጻፍና የባለሥልጣናትን ስም በማጥፋት ነበር፡፡ ተመስገን እስሩን የጨረሰው ከትናንት በስቲያ ጥቅምት 3 ቀን 2010 ቢሆንም ባልታወቀ ምክንያት ማረሚያ ቤቱ ታራሚውን ሊፈታው ፈቃደኛ አልነበረም፡፡
በዚህም የተነሳ ተመስገን የረሀብ አድማ ጀምሮ የነበረ ሲሆን፣ ዛሬ ጠዋት ላይ ግን እንዲፈታ ተደርጓል፡፡

የጋዜጠኛ ተመስገን ክስ የተጀመተው የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ ከመሞታቸው በፊት ቢሆንም፣ እርሳቸው ሲሞቱ ክሱ ለተወሰነ ጊዜ ተቋርጦ ነበር፡፡ ሆኖም ዓቃቤ ሕግ ክሱን በድጋሚ አስነስቶት ነው ተመስገን የሦስት ዓመት እስር የተፈረደበት፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ታዋቂው የኤሌክትሮኒክስ ብራንድ አይቴል የስትራቴጂ ለውጥ አካል የሆነውን አዲስ አርማ እና መለዮ ይፋ አደረገ።

በአለማችን ታዋቂ ከሆኑት የኤሌክትሮኒክስ ብራንዶች መካከል አንዱ የሆነው እና...

የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ጥሪ ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ

ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ የሸገር አነስተኛ የፋይናንስ...

[የክቡር ሚኒስትሩ ጸሐፊ፣ የሌላ ሚኒስትር ጸሐፊ ከሆነችው የቅርብ ወዳጇ ጋር በስልክ እየተጨዋወቱ ነው]

አንቺ ግን ምን ሆነሽ ነው? ጠፋሁ አይደል? ጠፋሁ ብቻ?! ምን ላድርግ ብለሽ...

በሱዳን ላይ ያጠላው የመከፋፈል ዕጣና ቀጣናዊ ተፅዕኖው

የሱዳን ጦርነት ስምንተኛ ወሩን እያገባደደ ይገኛል፡፡ ጄኔራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን...