Friday, June 2, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርትያያ ቱሬ ለአራተኛ ጊዜ የአፍሪካ ምርጥ ተጨዋች ተብሎ ተመረጠ

ያያ ቱሬ ለአራተኛ ጊዜ የአፍሪካ ምርጥ ተጨዋች ተብሎ ተመረጠ

ቀን:

ኮትዲቯራዊው ያያ ቱሬ የአፍሪካ የዓመቱ ምርጥ የእግር ኳስ ተጨዋች ተብሎ ለተከታታይ አራተኛ ጊዜ አሸናፊ ሆኗል፡፡ የእንግሊዙ ማንቸስተር ሲቲ አማካይ እ.ኤ.አ. የ2014 ምርጥ የአፍሪካ አሸናፊ በመሆን በናይጄሪያ ሌጉስ በተደረገው ሥነ ሥርዓት ላይ ሽልማት ማግኘቱን ካፍ ይፋ አድርጓል፡፡ ያያ ቱሬ እ.ኤ.አ. በ2011፣ በ2012 እና በ2013 አሸናፊ መሆኑ ይታወሳል፡፡ ከእሱ በፊት ካሜሮናዊው ሳሙኤል ኤቶ እ.ኤ.አ. በ2003፣ በ2005 እና በ2010 ማሸነፉ አይዘነጋም፡፡ ያያ ቱሬ ከተፎካካሪዎቹ 175 ድምፅ አግኝቶ አሸናፊ መሆኑ ሲገለጽ፣ የጋቦኑ አማካይ ኦባሚያንግ 120 ድምፅ፣ ናይጄሪያዊው ግብ ጠባቂ ኢኒያማ 105 ድምፅ በማግኘት ሁለተኛና ሦስተኛ ደረጃ በመሆን የአፍሪካ ምርጦች ሆነዋል፡፡ የብሔራዊ ቡድን አሠልጣኞች፣ የቴክኒክ ዳይሬክተሮችና ከካፍ ጋር ግንኙነት ያላቸው የስፖርት ማኅበራት መሪዎች በሰጡት ድምፅ መሠረት የአፍሪካ የዓመቱ ምርጥ ብሔራዊ ቡድን በመባል የአልጄሪያ ብሔራዊ ቡድን አሸናፊ ሆኗል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በአዲስ አበባ በድምቀት ተከበረ

የአዛርባጃን ኤምባሲ  የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በትላንትናው ዕለት አከበረ። ሰኞ...

የመንግሥትና የሃይማኖት ልዩነት መርህ በኢትዮጵያ

እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አገሮች የሃይማኖት ተቋማት አዎንታዊ ሚና የጎላ...

ሐበሻ ቢራ ባለፈው በጀት ዓመት 310 ሚሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን አስታወቀ

የአንድ አክሲዮን ሽያጭ ዋጋ 2,900 ብር እንዲሆን ተወስኗል የሐበሻ ቢራ...