Monday, May 29, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርትየስፖርት ቱሪዝምን እንደሚያስፋፉ የተነገረለት ውድድር በወንጪ ሐይቅ ላይ ይካሄዳል

የስፖርት ቱሪዝምን እንደሚያስፋፉ የተነገረለት ውድድር በወንጪ ሐይቅ ላይ ይካሄዳል

ቀን:

ለሦስተኛ ጊዜ በሚካሄደውና ገቢው ሙሉ ለሙሉ ለበጎ አድራጎት ሥራ ታስቦ በየዓመቱ የሚካሄደው ስፖርታዊ ውድድር ጥር 17 ቀን 2007 ዓ.ም. በወሊሶ ከተማ አቅራቢያ በሚገኘው ወንጪ ሐይቅ ላይ ይካሄዳል፡፡ 300 የሚደርሱ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ሠራተኞችና ሌሎች ዜጎችን በሚያሳትፈው ውድድር እንደሚካፈሉ ተገልጿል፡፡ የውድድሩ አዘጋጆች እንደገለጹት፣ ውድድሩ የስፖርት ቱሪዝምን በአገሪቱ እንዲስፋፋ ከማገዝ ባለፈ ገቢውን ለተለያዩ የበጎ አድራጎት ሥራዎች ማዋል መቻሉ ቦታ እንደሚያሰጠው፣ ዘንድሮም የካቲት 12 ሆስፒታል ውስጥ በአዲስ መልኩ ሊገነባ ለታሰበው የሕፃናት ድንገተኛ ሕክምና ክፍል የውድድሩን ገቢ እንደሚጠቀምበት ተገልጿል፡፡ በመዝናኛ እንቅስቃሴዎችና የአካል ብቃትን በሚያሳድጉ ስፖርቶች ታጅቦ የሚካሄደው ውድድር ለአሸናፊዎቹ ሽልማት በማበርከት እንደሚጠናቀቅ ተገልጿል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የመስቀል አደባባይ የመግቢያ ክፍያ ለምን?

ወጣቶች፣ ሕፃናትና አረጋውያን ሳይቀሩ መንፈሳቸውን የሚያድሱበት እንዲሁም ሐሳባቸውን በነፃነት...

በሕገ መንግሥቱ የተዋቀረው ‹‹የብሔር ፖለቲካ›› እና ‹‹ሥርዓቱ›› ያስከተለው መዘዝና መፍትሔው

(ክፍል አራት) በዓቢዩ ብርሌ (ጌራ) ባለፈው ጽሑፌ (በክፍል ሦስት) አሁን ያለው...

የኢትዮጵያ ኅብረተሰብና የመንግሥት መሪ ምሥል

በበቀለ ሹሜ በ2015 ዓ.ም. መጋቢት ወር ውስጥ ይመስለኛል በ‹ሸገር ካፌ›...

ዩኒቨርሲቲዎችን ራስ ገዝ ያደረገው አዋጅ የፍትሐዊነት ጥያቄ አስነሳ

በቀጣዮቹ ሁለት ዓመታት ስምንት ዩኒቨርሲቲዎችን ራስ ገዝ በማድረግ ተቋማዊና...