Monday, December 4, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊየእንቦጭ አረምን ለማስወገድ የማሽን ግዥ ጨረታ ሊወጣ ነው

የእንቦጭ አረምን ለማስወገድ የማሽን ግዥ ጨረታ ሊወጣ ነው

ቀን:

በጣና ሐይቅ ላይ የተንሰራፋውን የእንቦጭ አረም ለማስወገድ የማሽን ግዥ ጨረታ ሊወጣ መሆኑ ታወቀ፡፡

የአማራ ክልል የአካባቢ፣ ደንና ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር በላይነህ አየለ (ዶ/ር) ለሪፖርተር እንደተናገሩት፣ ከ2004 ዓ.ም. ጀምሮ በጣና ሐይቅ ላይ የተንሰራፋውን የአንቦጭ አረም በዘላቂነት ለማስወገድ የማሽን ግዥ ዓለም አቀፍ ጨረታ ሊወጣ ነው፡፡

በክልሉ መንግሥት፣ በበጎ ፈቃደኛ ወጣቶችና በክልሉ ውስጥ ባሉ ዩኒቨርሲቲዎች የእንቦጭ አረም ከተከሰተ ወዲህ ለመከላከል ጥረት እየተደረገ ቢሆንም፣ እስካሁን ድረስ ሙሉ በሙሉ ሐይቁን መታደግ እንዳልተቻለ ተናግረዋል፡፡ ችግሩን በዘላቂነት ለመከላከልና ጣናን ከተጋረጠበት ፈተና ለመታደግ፣ የክልሉ መንግሥት ከለጋሽ ድርጅቶችና ከፌዴራል መንግሥት ጋር በመሆን ማሽኑን ለመግዛት ተወስኗል፡፡

የክልሉ መንግሥት የችግሩን አሳሳቢነት በመገንዘብ በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ በጅቶ እየተንቀሳቀሰ መሆኑ፣ በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው የሚመራው የእንቦጭ መከላከያ ኮሚቴ እዚህ ውሳኔ ላይ መድረሱን ለማወቅ ተችሏል፡፡

የክልሉ መንግሥት ጨረታው እንዲወጣ ለሚመለከተው የፌዴራል መንግሥት ማስተላለፉን ዋና ዳይሬክተሩ ለሪፖርተር አረጋግጠዋል፡፡

ነገር ግን ጨረታው መቼ ወጥቶ መቼ እንደሚከፈትና ዝርዝር የጨረታ ሒደቱ እንዴት እንደሆነ ለማወቅ አልተቻለም፡፡

 

 

 

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

በዓለም አቀፍ ደረጃ ሕይወታቸውን በኤድስ ምክንያት ላጡ ሰዎች 35ኛ ዓመት መታሰቢያ

ያለፍንበትን እያስታወስን በቁርጠኝነት ወደፊት እንጓዝ - በኧርቪን ጄ ማሲንጋ (አምባሳደር) በየዓመቱ...

እዚያ ድሮን… እዚህ ድሮን…

በዳንኤል ካሳሁን (ዶ/ር) ተዓምራዊው የማዕበል ቅልበሳ “በሕግ ማስከበር” ዘመቻው “በቃ የተበተነ...

ለፈርጀ ብዙ የማንነት ንቃተ ህሊናችን የሚጠቅሙ ጥቂት ፍሬ ነገሮች

በበቀለ ሹሜ ከጨቅላነት ጅምሮ ያለ የእያንዳንዳችን የሰብዕና አገነባብ ከቤተሰብ እስከ...