Thursday, November 30, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ፍሬከናፍር‹‹አያቴ የዛሬ 50 ዓመት በረገጣት መሬት ታሪክን በመድገሜ ደስተኛ አድርጎኛል፡፡››

‹‹አያቴ የዛሬ 50 ዓመት በረገጣት መሬት ታሪክን በመድገሜ ደስተኛ አድርጎኛል፡፡››

ቀን:

ኢትዮጵያን እየጎበኙ ያሉት የኖርዌይ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት አልጋ ወራሽ ልዑል ሃኮን ማገኑስ፣ ፕሬዚዳንት ሙላቱ ተሾመ በብሔራዊ ቤተመንግሥት ጥቅምት 28 ቀን 2010 ዓ.ም. የክብር አቀባበል ባደረጉላቸው ጊዜ የተናገሩት፡፡

ፕሬዚዳቱና ልዑል አልጋ ወራሹ ሰባት አሠርታት ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ወደ አዲስ ምዕራፍ ለማሸጋገር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ የመከሩ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ ከኖርዌይ ጋር ያላትን ግንኙነት በሁሉም ዘርፎች ለማሳደግ ዝግጁ መሆኗን ፕሬዚዳንት ሙላቱ ተናግረዋል ኢትዮጵያ በገነባቻቸውና በግንባታ ላይ ባሉ ሰፋፊና ምቹ የኢንዱስትሪ ዞኖች፥ የኖርዌይ ባለሃብቶች መጥተው በተለያዩ የኢንቨስትመንት መስኮች ቢሰማሩ ውጤታማ እንደሚሆኑም ሳይናገሩ አላለፉም፡፡ ባለቤታቸው ልዕልት ሜቲ ማሪት ጋር የተገኙት ልዑል ሃኮን በበኩላቸው፣ 51 ዓመት በኋላ በንጉሣዊ ቤተሰብ ደረጃ  የተደረገው ጉብኝታቸው አገራቸው ከኢትዮጵያ ጋር ላላት ግንኙነት የላቀ ግምት ማሳያ ነው ብለዋል። እንደ አየር ንብረት ለውጥና ዘላቂ የልማት ግቦች ያሉ ዓለም አቀፍ ትልሞች በጋራ ለመሥራት እድል እንደሚፈጥሩም ገልጸዋል።

 

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የመቃወም ነፃነት ውዝግብ በኢትዮጵያ

ስሟ እንዳይገለጽ የጠየቀችው በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ የሾላ አካባቢ...

የሲሚንቶን እጥረትና ችግር ታሪክ ለማድረግ የተጀመረው አጓጊ ጥረት

በኢትዮጵያ በገበያ ውስጥ ለዓመታት ከፍተኛ ተግዳሮት በመሆን ከሚጠቀሱ ምርቶች...

የብሔር ፖለቲካው ጡዘት የእርስ በርስ ግጭት እንዳያባብስ ጥንቃቄ ይደረግ

በያሲን ባህሩ በሪፖርተር የኅዳር 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ዕትም “እኔ...