Tuesday, November 28, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናየንግድ ምዝገባ አዋጁ በተሻሻለ በዓመቱ በድጋሚ ሊሻሻል ነው

የንግድ ምዝገባ አዋጁ በተሻሻለ በዓመቱ በድጋሚ ሊሻሻል ነው

ቀን:

በ2006 ዓ.ም. ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቦ ለሁለተኛ ጊዜ ማሻሻያ የተደረገበት የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አዋጅ ለሦስተኛ ጊዜ ሊሻሻል መሆኑ ተሰማ፡፡

የንግድ ሚኒስቴር አዋጁን ለመተግበር በርካታ መሰናክሎች እየገጠሙት በመሆኑ፣ አዋጁን እንዲመረምር ያቋቋመው ኮሚቴ የአዋጁን ችግሮች ለይቶ ማውጣቱ ታውቋል፡፡ በዚህ መሠረትም አዋጁ እንዲሻሻል ሐሳብ ማቅረቡን ከንግድ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡

በርካታ ሰዎች የንግድ ስያሜ ይዘው ለማስመዝገብ ቢመጡም በተደጋጋሚ እየወደቀባቸው በመቸገራቸው የተፈጠረውን ቅሬታ ለማጣራት ባደረገው ሙከራ፣ ከንግድ ምልክትና ስያሜ ጋር በተያያዘ በርካታ የሚጣረሱና ለትርጉም ክፍት የሆኑ አንቀጾች እንዳሉበት የተቋቋመው ኮሚቴ ማረጋገጡን መረጃው ያመለክታል፡፡ በመሆኑም በቅርቡ የማሻሻያ ረቂቁ ተሠርቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት፣ ከዚያም ለተወካዮች ምክር ቤት የአሠራር ሒደቱን ተከትሎ እንደሚቀርብ ለማወቅ ተችሏል፡፡

በተባለው መሠረት ማሻሻያው ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሚቀርብ ከሆነ፣ በተሻሻለ በዓመቱ በድጋሚ ለመሻሻል የቀረበ አዋጅ ያደርገዋል፡፡ አዋጁ በ2006 ዓ.ም. ለፓርላማ እንዲቀርብ የተደረገው ከዳግም ምዝገባ ጋር የተፈጠረውን ችግር ለማስተካከል ነበር፡፡

ይኸው አዋጅ በ2004 ዓ.ም. መጨረሻ ላይም ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቦ ማሻሻያ ተደርጐበት ነበር፡፡ በዚህ ወቅት ደግሞ ማሻሻያ የተደረገበት ከፈቃድ ማደስ ጋር ተያይዞ የተቀመጠውን የጊዜ ገደብ ከጉምሩክ አዋጁ ጋር ለማጣጣም ሲባል መሆኑን የአዋጁ ማብራሪያ ያመለክታል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ለሲኒመር ትሬዲንግ አ/ማ አባላት በሙሉ የጠቅላላ ጉባኤ የስብሰባ ጥሪ

ለሲኒመር ትሬዲንግ አ/ማ አባላት በሙሉ የጠቅላላ ጉባኤ የስብሰባ ጥሪ ሲኒመር ትሬዲንግ...

የባህር በር በቀጣናዊ ተዛምዶ ውስጥ

በበቀለ ሹሜ መግቢያ በ2010 ዓ.ም. መጋቢት ማለቂያን ይዞ ዓብይ አህመድ በጠቅላይ...

ሥጋት ያስቀራል ተብሎ የሚታሰበው የጫኝና አውራጅ መመርያ

በአዲስ አበባ ከተማ በሕገወጥ መልኩ በመደራጀት ማኅበረሰቡ ላይ እንግልትና...

ማወቅ ወይስ አለማወቅ – ድፍረት ወይስ ፍርኃት?

በአሰፋ አደፍርስ ወገኖቼ ፈርተንም ደፍረንም የትም አንደርስምና ለአገራችን ሰላምና ክብር...