- Advertisement -

‹‹ሙዚቃ ሁሉንም እንዲናገር እናደርጋለን›› ሙዚቀኛ ሚና ጊርጊስ

የዘንድሮው የዘ ናይል ፕሮጀክት የሙዚቃ ድግስ መዳረሻውን አሜሪካ አድርጓል፡፡ 13 ሙዚቀኞች የተካተቱበት ቡድኑ በአሜሪካ የተለያዩ ከተሞች ኮንሰርት ያቀረበ ሲሆን፣ ሲምፓዝየሞችም ተካሂደዋል፡፡

የናይል ፕሮጀክት ድረ ገጽ እንደሚያሳየው፣ አባላቱ ከሙዚቃ ኮንሰርቶች በተጨማሪ በስታንፎርድና ቤርክሊ ‹‹ዘ ናይል ኤንድ አፍሪካን አይደንቲቲ፤››፣ ‹‹ሚውዚክ ኮላቦሬሽን ኤንድ ዋተር ኮኦፕሬሽን›› እና ‹‹ፉድ አሎንግ ዘ ናይል›› በሚሉ ርእሶች ወርክሾፖች ተካሂደዋል፡፡ በወርክሾፑ በናይል ተፋሰስ አገሮች መካከል የነበረውና ያለው ውዝግብ ተነስቷል፡፡ መድረክ ላይ የሚያቀርቧቸው ሙዚቃዎች ከዳሰሷቸው ርዕሰ ጉዳዮች በተጨማሪ ስለቅኝ ግዛትና ፆታዊ ጉዳዮች ውይይት ተደርጓል፡፡

 ዘ ናይል ፕሮጀክት ኢትዮጵያን ጨምሮ ከአሥር የዓባይ ተፋሰስ አገሮች በተውጣጡ ሙዚቀኞች የተዋቀረ ነው፡፡ መሥራቾቹ ግብፃዊው ኢትኖሚውዚኮሎጂስት ሚና ጊርጊስና ኢትዮጵያዊቷ መክሊት ሐደሮ ናቸው፡፡ በፕሮጀክቱም ዓባይ ወንዝ ያስተሳሰራቸው የሱዳን፣ የደቡብ ሱዳን፣ የኤርትራ፣ የኬንያ፣ የታንዛኒያ፣ የኡጋንዳ፣ የታንዛኒያ፣ የሩዋንዳ፣ የብሩንዲና የኮንጎ ሙዚቀኞችን አሰባስበዋል፡፡

ከመሥራቾቹ አንዱ ሚና እንደሚለው፣ ውይይቱ ያስፈለገው ከዓባይ ተፋሰስ አገሮች ውዝግብ ጀርባ ያለው እውነታ እንዲታወቅ ነው፡፡ ‹‹ከፅንሰ ሐሳብ ባለፈ አሁን የሚታየውን ሁነት መነሻ ሁሉም እንዲገነዘብ እንፈልጋለን፤ ከዓባይ ጋር ተያይዘው በሚመጡ ውዝግቦች የእኛ የናይል ተፋሰስ አገሮች ተወላጆች ሚና ምንድን ነው? የሚለውም መታወቅ አለበት፤›› ብሏል፡፡

ሚና አፍሪካዊ ማንነት ላይ የሚነሱ ጥያቄዎችን አንስቷል፡፡ እንደ ምሳሌ ግብፃውያን እንደ ዓረቦች እንደሚቆጠሩ ጠቅሶ፣ መሰል የማንነት ጥያቄዎች የዓባይን ጉዳይ ያወሳስቡታል ብሏል፡፡ እንደእሱ ገለጻ፣ ሙዚቀኞቹ ወደ መድረክ ሲወጡ የማንነትና የውኃ ጥያቄ ጋብ ይላል፡፡ ‹‹ሙዚቃ ሁሉንም እንዲናገር እናደርጋለን፤›› ሲል የመድረኩን ስሜት ይገልጸዋል፡፡ የዓባይ ተፋሰስ አገሮች ሙዚቀኞችን በአንድ መድረክ መመልከት ለብዙዎች እንደሚያስደስት ሳይጠቅስም አላለፈም፡፡

የሊንከን ሴንተር እንዳስታወቀው፣ ልዩ ጥምረት የሚታይበት ናይል ፕሮጀክት ሙዚቀኞች በናይል ተፋሰስ አገሮች መካከል ያለውን ትስስር የሚያሳዩ ሙዚቃዎች አስደምጠዋል፤ ተጣምረው ምሥራቅ አፍሪካዊ ድባብ ፈጥረዋል፡፡ የተሳተፉት ኢትዮጵያውያን መክሊት ሐደሮ፣ እንድሪስ ሐሰን፣ ዳዊት ሥዩም፣ ሰላምነሽ ዘመነ፣ ዮርጋ መስፍን፣ መኳንንት መለሰና አሥራት አያሌው ናቸው፡፡

- Advertisement -

ናይል ፕሮጀክት እ.ኤ.አ. በ2013 ‹‹አስዋን›› የተሰኘ አልበም አሳትሟል፡፡ ሱዳናዊው የማሳንኮፕ (የሱዳን ባህላዊ ሙዚቃ መሣሪያ) ተጫዋች አሕመድ ሰይድ አቡአማን እና ግብፃዊው ቫዮሊን ተጨዋች አልፍሬድ ጋሚል ጥምረት የታየበት ‹‹ጎንግዋብ›› የተሰኘ ዘፈንም ተወዳጅ ነው፡፡

እነዚሁ ከተለያዩ አገሮች የተውጣጡት የናይል ሙዚቃ ፕሮጀክት አባላት ቀጣይ ሥራቸውን የፊታችን መጋቢት 10 እና 11 ቀን 2007 ዓ.ም. በሊንከን ሴንተርና ፔስ ዩኒቨርሲቲ እንደሚያቀርቡ ታውቋል፡፡

- Advertisement -

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን

ከ ተመሳሳይ አምዶች

የመገለጡ ቀን እና ትውፊቱ

ከአንድ ሺሕ ዘጠኝ መቶ ሰማንያ ስድስት ዓመታት በፊት በዛሬዋ ቀን ማለትም ጥር 11 ቀን 31 ዓ.ም. (5531 ዓመተ ዓለም) ሰማያዊው በመሬታዊው እጅ የተጠመቀበት ነው፡፡ እግዚእ...

‹‹አሞራው ካሞራ››

‹‹በቅዳሴው ቦታ ቀለሃ ሲዘመር፣ እንዴት ሰንብተሻል እናትዋ ጎንደር፡፡ አገር እንደዋዛ ናፍቆት እንደዋዛ የእነ አሞራው አገር የመይሳው ካሳ አዘዞ ድማዛ፡፡ ከዳሽን ላይ ፈልቆ ቀድታ ያጠጣችው የነካትን ሁሉ አቃጥላ ፈጀችው፡፡›› ድምፃዊ አስቻለው ፈጠነ...

የእንግሊዝኛ አንባቢ ያገኘው ‹‹ኦሮማይ››

ሰሞኑን የምዕራቡን ሚዲያ የተቆጣጠረው መጽሐፋዊ ዜና የስመ ጥሩ ደራሲ በዓሉ ግርማ ለመሰወሩ ሰበብ የሆነበትን ታዋቂው ‹‹ኦሮማይ›› ልቦለዱ በሀገረ እንግሊዝ በእንግሊዝኛ ታትሞ መቅረቡ ነው፡፡ ከአማርኛ ወደ...

ወፎችና የሰው ልጅ ምንና ምን ናቸው?

በሔኖክ ያሬድ የሰው ልጆችና ወፎች የሚጋሯቸው፣ የሚያገናኛቸው ነጥቦች መኖራቸውን ጸሐፍት ይጠቅሳሉ። በአስደናቂ መልኩ ከተጠቀሱት መካከል  ነፃነትና ፍለጋ የጋራ ባህሪያት ሁነው መጥተዋል። ስለ አዕዋፋትና ሰዎች ተዘምዶ...

በዓል አድማቂው ‹‹ሁራ ሰለስተ››

ወርኃ ታኅሣሥና ጥር በክርስቲያኖች ዘንድ በትውፊታቸው መሠረት የሚያከብሯቸው በዓላት ልደት፣ ጥምቀት፣ አስተርእዮ በድምቀታቸው ለየት ይላሉ፡፡ ከዘመነ ልደት እስከ ዘመነ አስተርእዮ ከባህላዊ መገለጫዎች ጋር ከሚከበርባቸው...

ሙዚየምነትን የተቀዳጀው ብሔራዊ ቤተመንግሥት

የመጨረሻው የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ሥላሴ (1923-1967) የነገሡበትን የብር ኢዮቤልዩ በዓል ለማክበር የተገነባው ዘመናዊ ቤተ መንግሥት የተ ጠናቀቀው በ1947 ዓ.ም. ነበር። 25ኛ...

አዳዲስ ጽሁፎች

መንግሥት ገቢ ከመሰብሰብ ባሻገር ለሕዝብ ኑሮ ትኩረት ይስጥ!

የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ማደግ ያለበት በተገኘው ቀዳዳ ሁሉ ከሚሰበሰብ ታክስ ብቻ ሳይሆን ከግብርና፣ ከኢንዱስትሪ፣ ከማዕድን፣ ከአገልግሎትና ከሌሎች ሀብት አመንጪ ዘርፎች ጭምር ነው፡፡ በአሁኑ ጊዜ ቁጥራቸው...

የኢትዮጵያን ትንሳዔ ለማብሰርና ለመከወን ምን እናድርግ?

በጌታነህ አማረ ኢትዮጵያ ማለት ታላቅ አገር ቀደምት የሰው ዘር መገኛና የሥልጣኔ ባለቤት የሆነች አገር እንደነበረች ታሪክ ሲያወሳን ይኖራል። በዚያውም ልክ ይህች ታላቅ ነበረች የምትባል አገር...

የምድራችን (የሰው ልጆች) ተማፅኖ — አረንጓዴ ፖለቲካ!

(ወጥመዶችና ማምለጫችን) በታደሰ ሻንቆ የወጥመዶች ዓለም በአፍሪካ ቀንድ አገሮች ዘንድ ያሉ ውዝግቦችና ግጭቶች ምንም ተቀባቡ ምን፣ መሬትን ውኃን አፈርን ማዕድናትን ንግድንና መሰል ጥቅሞችን የተመለከቱ ናቸው፡፡ በእነዚህ...

‹‹መንግሥት ከሁሉም ነገር በላይ ቅድሚያ ሰጥቶ የኢኮኖሚ ጫናውን ለመቀነስ የነዳጅ ድጎማውን መቀጠል ይኖርበታል›› ሰርካለም ገብረ ክርስቶስ (ዶ/ር)፣  የነዳጅ ዘርፍ ከፍተኛ ባለሙያ

የነዳጅ ግብይት ሥርዓትን ለመዘርጋትና ለመቆጣጠር ያስችላል የተባለ አዲስ አዋጅ ባለፈው ሳምንት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፀድቋል፡፡ በኢትዮጵያ በነዳጅ ሥርጭት ግብይትና በአጠቃላይ በዘርፉ ያሉትን ማነቆዎች...

ስለካፒታል ገበያ ምንነትና ፋይዳ ያልተቋረጠና የተብራራ መረጃ ማድረስ ያሻል!

የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ በይፋ ሥራ ጀምሯል፡፡ አገራዊ ኢኮኖሚውን ከመደገፍና ለተለያዩ ኢንቨስትመንቶች የሚውል ካፒታል ለማሰባሰብ እንደ አንድ አማራጭ የሚወሰድና ለኢትዮጵያ እንደ አዲስ ምዕራፍ የሚታይ ዕርምጃ...

ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ በጀት የተያዘለት የሥነ ተዋልዶ ጤና ፕሮጀክት ይፋ ሆነ

በኢትዮጵያ በተለይ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በተከሰቱ ጦርነቶችና ግጭቶች ምክንያት እየተስተጓጎለ የመጣውን የሥነ ተዋልዶ ጤና አገልግሎት መልሶ ለማጠናከር ያስችላል የተባለ የ1.28 ቢሊዮን ብር ፕሮጀክት ይፋ...
[the_ad id="124766"]

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን