Wednesday, October 4, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርትየአይኦሲ ምክትል ፕሬዚዳንት የኢትዮጵያን ስፖርት እንደሚያግዙ ተናገሩ

የአይኦሲ ምክትል ፕሬዚዳንት የኢትዮጵያን ስፖርት እንደሚያግዙ ተናገሩ

ቀን:

የዓለም አቀፍ ኦሊምፒክ ኮሚቴ (አይኦሲ) ምክትል ፕሬዚዳንት ሞሮኳዊቷ ናዋል ኤል ሞትዋኬልት ከ18 ወራት በኋላ በሚካሄደው የሪዮ ዴጂኔሮ ኦሊምፒክ ኢትዮጵያ ከአትሌቲክሱ በተጨማሪ በወርልድ ቴኳንዶ፣ በብስክሌትና በቦክስ ስፖርቶች ተሳትፎ ይኖራት ዘንድ የሙያና የቁሳቁስ ድጋፍ የሚሰጥበትን መንገድ እንደሚያመቻቹ ገለጹ፡፡

የኢትዮጵያን ኦሊምፒክ ኮሚቴ ጽሕፈት ቤት ባለፈው ሐሙስ ሞሮኳዊቷ ናዋል ኤል ከኦሊምፒክ ኮሚቴው ጽሕፈት ቤት ዳይሬክተር አቶ ታምራት በቀለና ከሌሎችም ኃላፊዎች ጋር ባደረጉት ውይይት ባለፈው ግንቦት የአይኦሲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ቶማስ ባች በኢትዮጵያ ተገኝተው የአገሪቱን ስፖርት ለማገዝ ቃል የገቡትን አጠናክረው እንዲቀጥሉበት የበኩላቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል፡፡

ኢትዮጵያ በኦሊምፒክ መድረኮች አመርቂና ተጨባጭ ውጤቶችን ከምታስመዘግብበት አትሌቲክስ በተጨማሪ ድጋፍና የሙያ እገዛ ቢደረግላቸው ውጤት እንደሚመጣባቸው የሚታመንባቸው እንደ ወርልድ ቴኳንዶ፣ ብስክሌትና ቦክስ እንዲሁም ለአትሌቶች ነፃ የትምህርት ዕድል (ስኮላርሺፕ)፣ ለአሠልጣኞችና ለሌሎችም የየዘርፉ ባለሙያዎች ዘመናዊና ሳይንሳዊ ሥልጠና ለመስጠት የአይኦሲ ፕሬዚዳንት ቃል ከገቡት ይጠቀሳል፡፡

የተገባውን ቃል እንደሚያውቁ የተናገሩት የአይኦሲ ምክትል ፕሬዚዳንቷ፣ ይኼው ተግባራዊ እንዲሆንና ከዚህ እንደተመለሱም ከፕሬዚዳንቱ ጋር በመነጋገር ድጋፍና ትብብሩ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ፍላጎታቸው መሆኑን እንደገለጹ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ አስታውቋል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

[ክቡር ሚኒስትሩ ወደ መኖሪያ ቤታቸው ሲገቡ ባለቤታቸው በቴሌቪዥን የሚተላለፈውን ዜና በመገረም እየተመለከቱ አገኟቸው]

ምንድነው እንዲህ ቀልብሽን የሳበው? ስለሰላም ኖቤል ሽልማት ዜና እየተመለከትኩ ነበር። እና...

የወሎ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ መመሥረትና የአማራ ክልል ጥያቄ

አማራ የኢሕአዴግ አንዱ መሥራችና አጋር ከሆነው ብሔረ አማራ ዴሞክራሲያዊ...

የሽንኩርት ዋጋ ሰማይ የነካበት ምክንያት ምንድነው?

ባለፉት ሁለትና ሦስት ሳምንታት የሸማቾችን ኪስ ካስደነገጡ መሠረታዊ ከሚባሉ...

የአዲስ አበባ ንግድ ምክር ቤት ኤግዚቢሽን ማዕከልን እንዲያስተዳድር የተሰጠው ኮንትራት ለምን ተቋረጠ?

በአዲስ አበባ ከተማ ለንግድ ትርዒት ዝግጅት ብቸኛ በመሆን የሚጠቀሰው...