Thursday, September 21, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜና‹‹ለደቡብ ሱዳን ሰላም ያ ሁሉ ጥሪያችን ሳይሰማ ከንቱ ቀርቷል›› ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ...

‹‹ለደቡብ ሱዳን ሰላም ያ ሁሉ ጥሪያችን ሳይሰማ ከንቱ ቀርቷል›› ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ

ቀን:

አዲስ አበባ ከየካቲት 24 ቀን 2007 ዓ.ም. ጀምሮ ሲደራደሩ የቆዩት የደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪርና የቀድሞ ምክትላቸው ሪክ ማቻር፣ ሲጠበቅ የነበረውን ውይይታቸው ባለመስማማት ተጠናቀቀ፡፡

ተደራዳሪዎቹ ያለውጤት ከተበተኑ በኋላ የወቅቱ የኢጋድ ሊቀመንበር ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ባወጡት መግለጫ፣ በሁለቱ ወገኖች አለመግባባት የተነሳ በአገሪቱ ከዓመት በላይ በቆየው ቀውስ ‹‹ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ያሳዝናታል›› ሲሉም ተናግረዋል

ኢጋድ በዚያች አገር ሰላም እንዲሰፈን ያደረገውን ያላሰለሰ ጥረት አንስተው፣ ይህ ጥረቱ ግን የተፈለገውን ውጤት አለማፍራቱን በመግለጫቸው ደጋግመው ገልጸዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትርይለ ማርያም ሁለቱ ወገኖች ትርጉም አልባው ግጭት እንዲያበቃ ስምምነት ላይ አለመድረሳቸው፣ ከፖለቲካም ሆነ ከሞራል አንፃር ተቀባይነት የሌለው ነው ብለዋል።

በዚህ አስቸጋሪ ጊዜ የኢትዮጵያዝብና መላው የኢጋድ አካባቢ ከደቡብ ሱዳናውያን ጎን መሆናቸውን ያረጋገጡት አቶይለ ማርያም  በቅርብ ጊዜ ውስጥም ደቡብ ሱዳን ያጣችውን ሰላሟን እንደምታገኝ ተስፋቸውን ሳይገልጹ አላለፉም፡፡

የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ)እስከ የካቲት 26 ቀን  ድረስ የሽግግር መንግሥት ለመመሥረት የሚያስችላቸውን ድርድር እንዲያጠናቅቁ ቀነ ገደብ አስቀምጦ እንደነበር ይታወሳል።

በመጪው ሐምሌ ወር ሁለቱ ወገኖች የሽግግር መንግሥት ለመመሥረት የገቡትን ስምምነት እንዲያከብሩ ጥረቱ እንደሚቀጥልም፣ አቶይለ ማርያም በመግለጫቸው ላይ ጠቁመዋል።

 

 

 

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ባለሙያዎች ኮሚሽን ሪፖርት ምን ይዟል?

ለአሜሪካ ድምፅ አማርኛ ዝግጅት የስልክ አስተያየት የሰጡ አንድ የደንበጫ...

መንግሥት በአማራ ክልል ለወደሙ የአበባ እርሻዎች ድጋፍ እንዲያደርግ ተጠየቀ

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአማራ ክልል የተፈጠረው ግጭትና አለመረጋጋት በቢዝነስ...

አምናና ዘንድሮ!

እነሆ መስከረም ጠብቶ በአዲስ መንፈስ ተሞልተን መንገድ ጀምረናል። ‹‹አዲስ...