- Advertisement -

እባብ አዳኞቹ ወፎች

የጎዳና ሯጮች (Road Runner) የሚባሉ ወፎች ስማቸውን ያገኙት ከመኪና ፊት ለፊት በመሮጣቸው ነው፡፡ የምድር ኩኩ (Ground Cuckoo) እና እባብ በል (Snake Eater) ሌላው ስማቸው ነው፡፡ እነኚህ ወፎች ራትል እባብ (Rattle Snake)ን ሲያጠቁ፣ ሲገሉና ሲመገቡ ይታያሉ፡፡ ወፎቹ እባቡን የሚያጠቁት ክንፋቸውን ዘርግተው ላባቸውን በመበተን ሲሆን፣ ይህም የእባቡን ጥቃት ከላባው አልፎ እንዳይሄድ ያደርገዋል፡፡ በመጨረሻም ጭንቅላቱን አግኝተው እባቡን ይመቱትና የጦርነቱ ፍጻሜ ይሆናል፡፡ የሚመገቡት የሚችሉትን ያህል ውጠው በመፍጨት ነው፡፡ የተረፈውን የእባቡን አካል ደግሞ እያንጀላጀሉ እስኪውጡት ድረስ ወዲያ ወዲያ ይዘዋወራሉ፡፡

ሌሎች ወፎች ጭልፊትና ንስር አልፎ አልፎ እባብ ይበላሉ፡፡ ነገር ግን ዝነኛው ገዳይ ጸሐፊ ወፍ (Secretary Bird) ነው፡፡ ስማቸውንም ያገኙት ላባቸው ወደ ኋላ ቀሰር ያለ በመሆኑና ይህም ከድሮዎቹ ጸሐፊዎች (የላባ ብዕር ከጆሮዎቻቸው ኋላ ሸጎጥ ያደርጉ ስለነበር) ጋር ስለሚያመሳስላቸው ነው፡፡

  • ማንይንገረው ሸንቁጥ ‹‹ባለአከርካሪዎች›› (2004 ዓ.ም.)

  

 

- Advertisement -

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን

ከ ተመሳሳይ አምዶች

ባለ ጥምዝ ቀንዱ አምባራይሌ

አምባራይሌ አጠቃላይ ቁመናው ከቀንዱ ጥምዝ ጋር የአጋዘን ይመስላል፡፡ በመጠኑ ግን አነሰ ያለ ነው፡፡ የወንዱ ክብደት ከ92 እስከ 108 ኪሎ ግራም፤ የሴቶቹ ደግሞ ከ56 እስከ 70 ኪግ ይሆናል፡፡

የአሳ ነባሪ ሆድ ዕቃ

ከአሳ ነባሪ ሆድ ዕቃ የሚወጣ የስብ ክምችት የመሰለ ነገር አምበርጊስ ይባላል፡፡ አምበርጊስ ከእንስሳው የሚወጣው በቀጥታ በሚመገበው ምግብ ምክንያት ሲሆን በተጨማሪም የእንስሳው መታመም ምልክትም ተደርጎ ይወሰዳል፡፡

ጎሪላ

በመጠን ትልቁ ኤፕ ጎሪላ ነው፡፡ ጎሪላ ከሁሉም የፕራይሜት ቡድኖች በመጠኑ ይልቃል፡፡ ከ4-8 የሚሆኑ ጠንካራ ሰዎችን ያህል ጥንካሬ አለው፡፡ ጎሪላዎች እጃቸው ረጅምና ከእግራቸው በላቀ ሁኔታ ጡንቻማ ነው፡፡

ጀርባ ጥቁር ቀበሮ

ጀርባ ጥቁር ቀበሮ (Black-backed Jackal) በብዙ የኢትዮጵያ ሥፍራዎች ይገኛል፡፡ ከታንዛኒያ እስከ ቀይ ባሕር፣ እንዲሁም በሶማሊያ ይገኛል፡፡ በተረፈ በብዙ ሌሎች የአፍሪካ ሥፍራዎች ባይገኝም በደቡባዊ አፍሪካ በሚገኙ አገሮች ይኖራል፡፡

እንቁላሎቿን ሆዷ ውስጥ የምትታቀፈው እንቁራሪት

እንቁላሎቿን ሆዷ ውስጥ የምትታቀፈው የአውስትራሊያ የእንቁራሪት ዝርያ (ጋስትሪክ ብሩዲንግ ፍሮግ) ያልተለመደ ዓይነት የመራቢያ ሥርዓት አላት፤ የዚህች እንቁራሪት ዝርያ ከ2002 ጀምሮ እንደጠፋ ይታሰባል የሚለው ጄደብሊው ዶት ኦርግ ድረ ገጽ ነው።

እንሽላሊቱ ኮሞዶ ድራጐን

ኮሞዶ ድራጐን የእንሽላሊት ዝርያ ነው፡፡ ከእንሽላሊት ዝርያዎች በትልቅነቱ የሚታወቀው ኮሞዶ፣ በማዕከላዊ ኢንዶኔዥያ ኮሞዶ ደሴት ላይ በብዛት ይኖራል፡፡ አንዱ ኮሞዶ ድራጐን እስከ 70 ኪሎ ግራም የሚመዝን ሲሆን፣ ርዝመቱም ከሁለት እስክ ሦስት ሜትር ይደርሳል፡፡ መጋዝ የመሰሉ 60 ጥርሶች አሉት፡፡ ጥርሶቹ በተደጋጋሚ እየወለቁ የሚበቅሉም ናቸው፡፡

አዳዲስ ጽሁፎች

የኢትዮጵያ ልሂቃን የፖለቲካ ባህል ከዕልቂትና ከውድመት አዙሪት እንዴት እንውጣ?

(የመጨረሻ ክፍል) በሰለሞን ኃይለ ማርያም (ዶ/ር) ባለፈው ሳምንት ጽሑፌ ስለፖለቲካ ባህል ጽንሰ ሐሳብ፣ ከኢትዮጵያ የልሂቃን የፖለቲካ ባህል ውስጥ ስም ማጥፋትን፣ ተቀናቃኝን ማጥቃትንና የመደራደርና የሰጥቶ መቀበል ባህል...

ኢትዮጵያ የአፍሪካን አጀንዳ በተመለከተ ምን ያህል አስተዋጽኦ ማድረግ ትችላለች?

በታደሰ ሻንቆ ኢትዮጵያ ትርጉም ያለው አስተዋጽኦ ለማድረግ የአፍሪካን 2063 ግቦች አጣቅሳ የተለየ ትልም መንደፍ አያስፈልጋትም፡፡ የውስጥ ሰላሟን ከማስተማመን ጋር አሁን የተያያዘችውን የትስስርና የግስጋሴ ፖሊሲ በማጎላመስ...

‹‹በጠመንጃ ተያይዘን እንወድቃለን እንጂ አብረን አንቆምም›› ፊልሰን አብዱላሂ፣ የሆርን ፒስ ኢንስቲትዩት መሥራችና ዳይሬክተር

የቀድሞዋ የሴቶች፣ ወጣቶችና ሕፃናት ሚኒስትር ፊልሰን አብዱላሂ አሁን ደግሞ ሆርን ፒስ ኢንስቲትዩት የተባለ በሰላም ላይ የሚሠራ ሲቪክ ማኅበር መሥርተው በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛሉ፡፡ ይህ ተቋም...

ነዳጅ ለመቅዳት እስከ ዕኩለ ሌሊት መሠለፍ የሚያበቃው መቼ ነው?

ያለመታደል ሆኖ በተደጋጋሚ እያጋጠሙን ለሚገኙ አንዳንድ ችግሮች ዘላቂ መፍትሔ ለማበጀት እየተቸገርን ነው። በተደጋጋሚ ለሚገጥሙን ችግሮች ጨከን ብሎ መፍትሔ ማምጣት ያለመቻላችን በራሱ ችግሮችን ለመፍታት አቅም...

‹‹ሕወሓት ሲፈልግ መንግሥት ሲፈልግ ፓርቲ ወይም ሕዝብ ነኝ ማለቱን ትቶ እንደ አንድ የፖለቲካ ፓርቲ መንቀሳቀስ አለበት›› ጌታቸው አሰፋ (ፕሮፌሰር)፣ ፖለቲካ ተንታኝ

ምርጫ ቦርድ ለሕወሓት የሰጠውና እስከ የካቲት 3 ቀን 2017 ዓ.ም. ድረስ ባሉት ቀናት ጠቅላላ ጉባዔ እንዲያደርግ የሚያስገድደው ማሳሰቢያ ቀነ ገደቡ ነገ ያበቃል፡፡ የካቲት 11...

‹‹አክሱም የአፍሪካዊ ሥልጣኔ በጨረፍታ››

በሽብሩ ተድላ ይህች ጽሑፍ መጠነኛ አስተያየት የምታቀርበው "AKSUM A glimpse into an African civilization by Hailu Habtu/Zamra Press.2024" (እኔ ርዕሱን "አክሱም የአፍሪካዊ ሥልጣኔ በጨረፍታ" ብዬ...
[the_ad id="124766"]

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን