Tuesday, October 3, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርትየእግር ኳስ ፌዴሬሽን ምክትል ፕሬዚዳንት የትግራይ ሴቶችንና ጠቅላይ ሚኒስትሩን ይቅርታ ጠየቁ

የእግር ኳስ ፌዴሬሽን ምክትል ፕሬዚዳንት የትግራይ ሴቶችንና ጠቅላይ ሚኒስትሩን ይቅርታ ጠየቁ

ቀን:

 የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ተክለ ወይኒ አሰፋ ባለፈው ሳምንት በተከናወነው የብሔራዊ ፌዴሬሽኑ ጠቅላላ ጉባዔ ላይ የመቐለ ሴቶችን በተመለከተ ለተናገሩትና ተቃውሞ ላስከተለባቸው አነጋገራቸው ይቅርታ መጠየቃቸው ታወቀ፡፡

አቶ ተክለ ወይኒ ኅዳር 4 ቀን 2010 ዓ.ም. በመቐለ ከተማ ፕላኔት ሆቴል ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት መግለጫ፣ ‹‹ባለፈው ዓርብ [ኅዳር 1 ቀን] የተናገርኩት ትክክል አልነበረም፡፡ የትግራይ ሴቶችን ከልቤ ይቅርታ እጠይቃለሁ፤›› ብለዋል፡፡ በሌላ በኩልም ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ብሔራዊ ፌዴሬሽኖችን መመራት ያለባቸው በስፖርቱ ባለፉ ባለሙያዎች መሆን እንደሚኖርባቸው ያስቀመጡት አቅጣጫ ላይ ለሰነዘሩት አስተያየትም አቶ ተክለ ወይኒ ይቅርታ መጠየቃቸው ተገልጿል፡፡

ክልሉ የምክትል ፕሬዚዳንቱን አ    አስተያየቶች ተከትሎ ክልሉ በዘንድሮው ምርጫ ዳግም ለሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልነት እንዲወዳደሩ ሰጥቷቸው የነበረውን ውክልና ሰርዟል፡፡ አቶ ተክለ ወይኒ የክልሉን ውሳኔ መቀበላቸውን በመግለጫቸው ተናግረዋል፡፡

በክልሉ ሴቶች ላይ የተሰነዘረውን አሉታዊ አስተያየት የትግራይ ሴቶች ማኅበር (ማደአት) በመቃወም ኅዳር 3 ቀን 2010 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ አቶ ተክለወይኒ በይፋ ይቅርታ እንዲጠይቁ ማሳሰቡ ይታወቃል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ተመድንና ዓለም አቀፋዊ ሕግን ከእነ አሜሪካ አድራጊ ፈጣሪነት እናድን!

በገነት ዓለሙ በእኔ የተማሪነት፣ የመጀመርያ ደረጃ ተማሪነት ጊዜ፣ የመዝሙር ትምህርት...

የሰላም ዕጦትና የኢኮኖሚው መንገራገጭ አንድምታ

በንጉሥ ወዳጅነው ፍራንክ ቲስትልዌይት የተባሉ አሜሪካዊ ጸሐፊ ‹‹The Great Experiment...

ድህነት የሀብት ዕጦት ሳይሆን ያለውን በአግባቡ ለመጠቀም አለመቻል ነው

በአንድነት ኃይሉ ድህነት ላይ አልተግባባንም፡፡ ብንግባባ ኖሮ ትናንትም ምክንያት ዛሬም...