Wednesday, September 27, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ፍሬከናፍርፍሬ ከናፍር

ፍሬ ከናፍር

ቀን:

‹‹አመፅ በማነሳሳት ወንጀል አቤቱታ የቀረበባቸው የናይጄሪያ ቀዳማዊት እመቤት በዓለም አቀፍ የወንጀል ፍርድ ቤት ምርመራ ይደረግባቸዋል››

የዓለም የወንጀል ፍርድ ቤት በናይጄሪያ ቀዳማዊት እመቤት ፔሸንስ ጆናታን ላይ በቀረበለት አቤቱታ መሠረት፣ አመፅ በማነሳሳት ድርጊት ምርመራ እንደሚያካሂድባቸው ከተናገረው የተወሰደ፡፡ የናይጄሪያ ጋዜጦች ባወጡት ዘገባ መሠረት፣ ቀዳማዊት አመቤት ጆናታን ደጋፊዎቻቸው የኦል ፕሮግሬሲቭ ኮንግረስ ፓርቲ አባላትን በድንጋይ እንዲደበድቡ አዘዋል፡፡ ይህንንም ድርጊት ፓርቲው ለዓለም አቀፉ ፍርድ ቤት አቤቱታ በማቅረቡ፣ ፍርድ ቤቱ የሴትየዋ ድርጊት መመርመር አለበት ብሏል፡፡ የዓለም አቀፍ ፍርድ ቤቱ ዓቃቤ ሕግ ፋቱ ቤንሱዳ፣ ፍርድ ቤቱ ቀዳማዊት እመቤት ጆናታንን መርምሮ ከመክሰስ አያመነታም ብለዋል፡፡ ‹‹ማንም ሰው ከምርጫ በፊት፣ ወቅትና በኋላ አመፅ የሚቀሰቅስ ከሆነ ይከሰሳል፤›› በማለት አስረድተዋል፡፡ ዘገባዎች እንደሚያስረዱት የገዥው ፒፕልስ ዴሞክራቲክ ፓርቲ ተቀናቃኝ ኦል ፕሮግሬሲቭ ኮንግረስ ፓርቲ አባላትን ‹‹ጊዜ ያለፈበት መድኃኒት›› ናቸው ከማለታቸው በተጨማሪ፣ በደጋፊዎቻቸው ድብደባ እንዲፈጸምባቸው ማዘዛቸው ቀዳማዊት እመቤት ጆናታንን እያስወቀሰ መሆኑ እየተገለጸ ነው፡፡ በምሥሉ ላይ የሚታዩት ቀዳማዊት እመቤት ፔሸንስ ጆናታን ናቸው፡፡

 

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የአማራ ክልል ወቅታዊ ሁኔታ

እሑድ ጠዋት መስከረም 13 ቀን 2016 ዓ.ም. የፋኖ ታጣቂዎች...

ብሔራዊ ባንክ ለተመረጡ አልሚዎች የውጭ አካውንት እንዲከፍቱ ለመጀመሪያ ጊዜ የፈቀደበት መመርያና ዝርዝሮቹ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሪ አጠቃቀምንና ተያያዥነት ያላቸው ጉዳዮችን...

እነ ሰበብ ደርዳሪዎች!

ከሜክሲኮ ወደ ዓለም ባንክ ልንጓዝ ነው። ሾፌርና ወያላ ጎማ...