Friday, December 8, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናየአማራና የትግራይ ሕዝቦች ውይይት ነገ ይጀመራል

የአማራና የትግራይ ሕዝቦች ውይይት ነገ ይጀመራል

ቀን:

የአማራ ክልልና የትግራይ ክልል የሕዝብ ለሕዝብ ውይይት መድረክ ቅዳሜ ኅዳር 9 ቀን 2010 ዓ.ም. በጎንደር ከተማ ሊካሄድ እንደሆነ የአማራ ክልል የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ንጉሡ ጥላሁን በግል ይፋዊ የፌስቡክ ገጻቸው ላይ ገለጹ፡፡

አቶ ንጉሡ “የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ከአጎራባች ክልሎች ጋር የሕዝብ ለሕዝብ መድረክ በመፍጠር በአብሮነትናአንድነት ላይ ምክክር ለማካሔድ ባቀደው መሠረት በነሐሴ ወር በመቀሌ ተካሂዶ የነበረው የአማራና የትግራይ ክልሎች ሕዝቦች የጋራ መድረክ ቀጣይ ክፍል በታሪካዊቷና የከተሞች እናት በመባል በምትታወቀው ጎንደር ከተማ ይጀመራል፡፡ምክክር መድረኩ እስከዳር 10 ቀን 2010 .. የሚቆይ ሲሆን፣ ከትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት 500 ያህል የሃይማኖት አባቶች፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ ምሁራን፣ አመራሮችና ልዩ ልዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች በምክክር መድረኩ ላይ ለመታደም ወደ ጎንደር በመጓጓዝ ላይ ናቸው፤” በፌስቡክ ገጻቸው ላይ ገልጸዋል፡፡

ከአማራ ክልል ብቻ 800 ተሳታፊዎች የሚገኙበት ይህ መድረክ ከሁለቱም ክልሎች 1300 ያህል ተሳታፊዎች ወደ ጎንደር ከተማ ዛሬ በመግባት ላይ ይገኛሉ፡፡

በነገውለት በሚጀመረው የምክክር መድረክ ላይየመወያያ ጽሁፍ ቀርቦ ውይይት ይደረጋል፤” ሲሉ ኃላፊው በፌስቡክ ገጻቸው ላይ ገልጸዋል፡፡

ከሁለት ሳምንታት በፊት በኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ለማ መገርሳ የተመራው ልዑክ የሕዝብ ለሕዝብ ውይይት ለማርደግ በባህር ዳር ከተማ ተገኝተው እንደነበር የሚታወስ ነው፡፡

 

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ታዋቂው የኤሌክትሮኒክስ ብራንድ አይቴል የስትራቴጂ ለውጥ አካል የሆነውን አዲስ አርማ እና መለዮ ይፋ አደረገ።

በአለማችን ታዋቂ ከሆኑት የኤሌክትሮኒክስ ብራንዶች መካከል አንዱ የሆነው እና...

የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ጥሪ ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ

ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ የሸገር አነስተኛ የፋይናንስ...

[የክቡር ሚኒስትሩ ጸሐፊ፣ የሌላ ሚኒስትር ጸሐፊ ከሆነችው የቅርብ ወዳጇ ጋር በስልክ እየተጨዋወቱ ነው]

አንቺ ግን ምን ሆነሽ ነው? ጠፋሁ አይደል? ጠፋሁ ብቻ?! ምን ላድርግ ብለሽ...

በሱዳን ላይ ያጠላው የመከፋፈል ዕጣና ቀጣናዊ ተፅዕኖው

የሱዳን ጦርነት ስምንተኛ ወሩን እያገባደደ ይገኛል፡፡ ጄኔራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን...