- Advertisement -

8100 ኤ ለግድቡ 84 ሚሊዮን ብር ገቢ አስገኘ

በኪነ ጥበቡ ታዋቂ የሆኑ ግለሰቦች፣ በመገናኛ ብዙኃን ያስተዋውቁት የነበረው የፅሑፍ መልዕክት መላኪያ 8100 ኤ፣ ለታላቁ ህዳሴ ግድብ የተጣራ 84 ሚሊዮን ብር ገቢ እንዳስገኘ ታወቀ፡፡ ባለፈው ስድስት ወር በሦስት ብር ክፍያ ‹‹ኤ›› ፊደልን ከተንቀሳቃሽ ስልኮቻቸው የላኩ ግለሰቦች በርካታ ስለነበሩ ገቢው እንደጨመረ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ሕዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሔራዊ ምክር ቤት ጽሕፈት ቤት የሚዲያና ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተሩ አቶ ፈቃዱ ከተማ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

እንደ ዳይሬክተሩ ገለጻ፣ በ8100 ኤ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ካደረጉ ድርጅቶች መካከል በአውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪና በኤሌክትሮኒክስ ዘርፍ ያሉ ባለሀብቶች ይጠቀሳሉ፡፡ ኢኳቶሪያል ቢዝነስ ግሩፕ፣ ማራቶን ሞተርስ ኢትዮ ኒኮንና ሌሎችም በመኪና ኢንዱስትሪ ያሉ ድርጅቶች እስከ 1.5 ሚሊዮን ብር የሚያወጡ መኪናዎችን አበርክተዋል፡፡

በተጨማሪ ስናፕ፣ አልታ፣ ሀሮን ኮምፒዩተርና ሌሎችም ድርጅቶች ለሽልማት የሚሆኑ ላፕቶፖችን ሰጥተዋል፡፡ አቶ ፈቃዱ ሪፖርተርን ጨምሮ ልዩ ልዩ ሚዲያዎችን 8100 ኤን በማስተዋወቅ እንዲሁም የኢትዮጵያ ቴሌኮምዩኒኬሽን በነፃ አጭር መልዕክት በመላክና የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በነፃ በማስተላለፍ አስተዋጽኦ አበርክተዋል ብለዋል፡፡

የተጠቀሱትን ተቋሞች ጨምሮ 1,200 ተቋሞች ለግድቡ ላበረከቱት አስተዋጽኦ የምሥጋና መርሐ ግብር ሚያዝያ 7 ቀን 2007 ዓ.ም. በሒልተን አዲስ ተካሂዷል፡፡ የታላቁ ህዳሴ ግድብ የመሠረት ድንጋይ የተቀመጠበትን አራተኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ በተሰናዳው ዝግጅት፣ ሽልማት የተሰጣቸው ለግድቡ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከቱ እንደሆኑ ተገልጿል፡፡

ሥነ ሥርዓቱ ላይ ተገኝተው ሽልማት ያበረከቱት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ሕዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሔራዊ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ደመቀ መኰንን፣ ‹‹ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን በመሰለ የሕዝብ ሕይወትና የአገር ገጽታ በሚቀይር ታሪካዊ ፕሮጀክት ላይ መሳተፍ በራሱ ሽልማት ቢሆንም፣ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደረጉትን መሸለም አስፈላጊ ነው፤›› ብለዋል፡፡

ግድቡ አሁን ካለበት ወሳኝ ደረጃ ላይ እንዲደርስ ሕዝቡ ላደረገው አስተዋጽኦ ምሥጋና አቅርበዋል፡፡ በገንዘብ፣ በፐብሊክ ዲፕሎማሲ፣ በአካባቢ ጥበቃና በሌላም መንገድ የሚደረገው ድጋፍ እንዲቀጥልም መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

- Advertisement -

 አቶ ፈቃዱ በበኩላቸው፣ ‹‹ሽልማቱ በሀብት፣ በጉልበትና በዕውቀት የላቀ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ተሰጥቷል፡፡ በእርግጥ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ በግድቡ ላይ ለነበረው ተሳትፎ ሽልማት ይገባዋል፡፡ ዕውቅናው መሰጠቱ ለተሸላሚዎች የሞራል ጥንካሬ የሚሰጥና ሌሎችንም ለተመሳሳይ ሥራ የሚያነሳሳ ይሆናል፤›› ሲሉ አስረድተዋል፡፡

8100 ኤ ቦንድ መግዛት የማይችሉ ግለሰቦችንም በግድቡ ሥራ እንዲሳተፉና ግድቡ የጋራ አጀንዳ ሆኖ በሕዝብ ልብ እንዲቆይ አስችሏል ብለዋል፡፡ በማስተዋወቅ ሥራው የተሳተፉ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎችን ‹‹የግድቡ የጀርባ አጥንት›› በማለት ገልጸው፣ ሕዝቡን ያነሳሱ ሥራዎችን እንዳቀረቡ ተናግረዋል፡፡

በሽልማቱ ከተካተቱ መካከል የተለያዩ የሙያ ማኅበራት፣ ግለሰቦች፣ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ይጠቀሳሉ፡፡ የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር፣ ሰርከስ ኢትዮጵያ፣ የፌዴራል ስፖርት ኮሚሽን፣ የአዲስ አበባ መምህራን ማኅበር፣ የኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ጽሕፈት ቤትና ብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ከተሸላሚዎቹ መካከል ናቸው፡፡ በተጨማሪ ባንኮች፣ ሙዚቀኞች፣ ኮሜዲያን፣ አትሌቶች፣ የማስታወቂያ ሥራ ድርጅቶች፣ ጥናታዊ ጽሑፎችን ያዘጋጁ ግለሰቦች፣ ባለሀብቶች እንዲሁም የሚዲያ ተቋሞች ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡

8100 ኤ ከጥቂት ጊዜ በኋላ እንደሚጀመርና በቅርብ 14 ዘፈኖች የያዘ የሙዚቃ አልበም ለግድቡ የሚውል ገቢ ለማስገኘት ለገበያ እንደሚቀርብ ለማወቅ ተችሏል፡፡   

  

- Advertisement -

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን

ከ ተመሳሳይ አምዶች

ለከተራና ጥምቀት በዓላት ትኩረት የሚሹት ለኮሪደር ልማት የተቆፋፈሩ መንገዶች

የዘንድሮ የጥምቀት በዓል በተለይ በአዲስ አበባ ለየት ባለ ጥበቃ የሚከበር ስለመሆኑ የአዲስ አበባ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ አስታውቋል፡፡ የደንብ ማስከበር ባለሥልጣንና ሌሎች አካላትም በዓሉ በሰላም...

ኢትዮጵያዊቷ ተማሪ የ2025 የሁዋዌ ዓለም አቀፍ አምባሳደር ሆና ተመረጠች

የሥላሴ ዩኒቨርሲቲ አራተኛ ዓመት የኮምፒዩተር ሳይንስ ተማሪ አሲያ ከሊፋ የሁዋዌ የ2025 የሲድስ ፎር ዘ ፊውቸር ዓለም አቀፍ አምባሳደሮች አንዷ ሆና ተመረጠች፡፡ ሁዋዌ ከመረጣቸው 12 አምባሳደሮች...

አገልግሎት የማይሰጡና 32 ሚሊዮን ብር ግምት ያላቸው ምግብና የንፅህና መጠበቂያ ምርቶች ተወገዱ

ባለፉት ስድስት ወራት ከ32 ሚሊዮን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው፣ የተበላሹ ምግቦችና የንጽሕና መጠበቂያ ምርቶች መወገዳቸውን፣ የአዲስ አበባ ከተማ ምግብና መድኃኒት አስተዳደር ቁጥጥር ባለሥልጣን...

የቤተሰብ ኃላፊነት የተሸከሙ ሕፃናት

በመማሪያና በለጋ ዕድሜያቸው የቤተሰብ ኃላፊነት ተጭኖባቸው ከትምህርት ገበታ ርቀው የሚቀሩ ሕፃናት በርካታ ናቸው፡፡ በቤተሰብ መበተን፣ ከቀዬ በመፈናቀልና በተለያዩ ችግሮች ምክንያት ሕፃናትና ታዳጊዎች ሲለምኑ፣ ሶፍትና...

ልሂቅ የምጣኔ ሀብት ባለሙያና ፖለቲከኛ በፍቃዱ ደግፌ (ዶ/ር) ሲታወሱ

የምጣኔ ሀብት (ኢኮኖሚክስ) ዕውቀትን እስከ ሦስተኛ ዲግሪ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢኮኖሚክስ ትምህርት ክፍል በከፍተኛ ደረጃ ያስተማሩ፣ ያማከሩ ነበሩ፡፡ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የነበራቸው የአገልግሎት ቁርጠኝነት...

በኮዬ ፈጬ ክፍለ ከተማ ጫማ ጠራጊዎች ያለ ደረሰኝ ግብር እየከፈልን ነው አሉ

በሸገር ከተማ ኮዬ ፈጬ ክፍለ ከተማ ወዴሳ ወረዳ በጫማ መጥረግ ሥራ ላይ የተሰማሩ ግለሰቦች ያለ ደረሰኝ በወር 2,700 ብር ግብር በመክፈል ላይ መሆናቸውን ተናገሩ፡፡...

አዳዲስ ጽሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ ቀኑን ሙሉ ከዋሉበት የሥራ አስፈጻሚ ስብሰባ ወደ መኖሪያ ቤታቸው ተመልሰው ከባለቤታቸው ጋር እያወጉ ነው]

የምን ስብሰባ ላይ ዋልኩ ነበር ያልከኝ? የሥራ አስፈጻሚ። የምን ሥራ አስፈጻሚ? የገዥው ሥራ አስፈጻሚ። ምን ገጥሟችሁ ነው የተሰበሰባችሁት? ለመረጠን ሕዝብ ቃል የገባናቸውን ተግባራት አፈጻጸም የምንገመግምበት የተለመደ ስብሰባ ነው። የገባችሁት ቃል...

ሕወሓትን አጣብቂኝ ውስጥ የከተተው መመርያ

በሁለት አንጃ ተከፍሎ የእርስ በርስ የቃላት ጦርነት ውስጥ የገባው ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) ልዩነቱን ትቶ ወደቀድሞው አንድነቱ በመመለስ የሚጠበቅበትን ጠቅላላ ጉባዔ የማድረግ አልያም...

ባንኮች እየፈጸሙት ያለው አቅርቦትንና ፍላጎትን ያላገናዘበ የውጭ ምንዛሪ ግዥ

የውጭ ምንዛሪ ግብይት በገበያ ዋጋ እንዲገበይ የወጣው ሕግ ተግባራዊ መሆን ከጀመረ ከሰባት ወራት በላይ አስቆጥሯል፡፡ ሕጉ ተግባራዊ በተደረገበት የመጀመርያው ቀን የአንድ ዶላር የምንዛሪ ዋጋ...

አሳረኛው ኑሮ!

የዛሬው ጉዞ ከቦሌ ወደ ፒያሳ ይሆን ዘንድ ግድ ሆኗል፡፡ ለምን? በኑሮ  ምክንያት፡፡ የታክሲ መሠለፊያው ወሬ የነዳጅ ጭማሪውን ተከትሎ ስለሚመጣው ተጨማሪ ታሪፍ ነው፡፡ ‹‹የእኛ ኑሮ...

የግለሰቦች ለመብታቸው ኃላፊነት አለመውሰድ ለአገር ያለው አደጋ

በያሬድ ኃይለመስቀል አንድ የማከብረው ኢኮኖሚስት አንድ መጽሐፍ እንዳነብ መራኝና ማንበብ ጀመርኩኝ። ይህንን መጽሐፍ ሳነበው ከዋናው ሐሳብ ወጣ ብሎ ስለ “የነፃ ተጓዦች ሀተታ” (The Free Rider...

‹‹የብድርና ቁጠባ ኅብረት ሥራ ማኅበራትን ኢኮኖሚያዊ አስተዋጽኦ ማጠናከር ያስፈልጋል›› አቶ ፍፁም አብርሃ፣ የአሚጎስ ብድርና ቁጠባ ኅብረት ሥራ ማኅበር መሥራችና ሥራ አስኪያጅ

አሚጎስ የብድርና ቁጠባ ኅብረት ሥራ ማኅበር ከተመሠረተ አሥራ ሁለት ዓመታት ሆኖታል፡፡ በእነዚህ ዓመታት 8,500 አባላትን ማፍራት ችሏል፡፡ አሚጎስ ስለተመሠረተበት ዓላማ፣ እያከናወናቸው ስለሚገኙ ተግባራት፣ የብድርና...
[the_ad id="124766"]

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን