- Advertisement -

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም የሥራ አፈጻጸም ሪፖርታቸውን ያቀርባሉ

 

  • የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን አፈጻጸም ያብራራሉ
  • በሶማሊያና በኦሮሚያ ክልሎች ስለተነሳው የድንበር ግጭት ያነሳሉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ የስድስት ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርታቸውን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ረቡዕ መጋቢት 7 ቀን 2009 ዓ.ም. ያቀርባሉ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የመንግሥታቸው የሥራ አፈጻጸም በየዘርፉ ምን ይመስል እንደነበር፣ የወደፊት አቅጣጫዎችን፣ ሊጠናቀቅ አንድ ወር ያህል ስለቀረው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፈጻጸምና ያስገኛቸው ውጤቶች ሪፖርት እንደሚያቀርቡ ለማወቅ ተችሏል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም በኦሮሚያና በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልሎች አዋሳኝ ድንበሮች ላይ እየታየ ስላለው ግጭት ማብራሪያ እንደሚሰጡ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም በጥር ወር መጨረሻ ላይ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ በሁለቱ ክልሎች አዋሳኝ ድንበሮች ላይ የተነሳው ግጭት አሳሳቢ እንደሆነ ገልጸው፣ በሁለቱም ክልሎች ውስጥ የሚገኙ የበታች አመራሮችን ተጠያቂ ማድረጋቸውን መዘገባችን ይታወሳል፡፡

ከሳምንት በፊት የኦሮሚያ ክልላዊ ምክር ቤት (ጨፌ) በዚሁ የድንበር ግጭት ላይ ተወያይቶ ችግሩ በሰላማዊ መንገድ እንዲፈታና የክልሉ ፖሊስ በአካባቢው የሚገኙ  ነዋሪዎች ደኅንነት እንዲጠብቅ ውሳኔ ማሳለፉን መዘገባችን አይዘነጋም፡፡

የጠቅላይ ሚኒስትሩን ሪፖርት በጠዋት ፕሮግራም የሚያዳምጠው ፓርላማው፣ ከቀትር በኋላ ውሎው ደግሞ የጂቡቲ ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኡመር ጊሌ ለኢትዮጵያ ሕዝብ የሚያደርጉትን ንግግር ያዳምጣል፡፡

- Advertisement -

ፕሬዚዳንቱ ንግግራቸውን የሚያደርጉት ለሕዝብ ተወካዮችና የፌዴሬሽን ምክር ቤቶች መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡ ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኡመር ጊሌ በኢትዮጵያና በጂቡቲ መካከል ስለተፈጠረው ኢኮኖሚያዊ ቁርኝትና ኢኮኖሚያዊ ውህደት አፅንኦት ሰጥተው ያብራራሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ከሁለት ዓመት በፊት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም በጂቡቲ ፓርላማ በመገኘት ለጂቡቲ ሕዝብ ንግግር ማድረጋቸው ይታወሳል፡፡ የኢትዮጵያና የጂቡቲ ሕዝቦች ወደፊት አንድ ሆነው ማየት ህልማቸው እንደሆነ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም በንግግራቸው ማስታወቃቸው ሪፖርተር ከሥፍራው መዘገቡ ይታወሳል፡፡ 

- Advertisement -

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን

ከ ተመሳሳይ አምዶች

በተያዘው ወር መጨረሻ  አዲስ ፖስፖርትና ቪዛ  ይፋ ይደረጋል ተባለ

በውጭ አገር የሚታተመውን ፓስፖርትና አገሪቱ ለውጭ ዜጎች የምትሰጠውን ቪዛ በአዲስ ይዘትና ኅትመት በአገር ውስጥ ታትሞ በተያዘው ወር የካቲት 2017 ዓ.ም. ይፋ እንደሚደረግ የኢሚግሬሽንና ዜግነት...

በውጭ አገር ለሚሰጥ ሕክምና የአገር ውስጥ ተወካይ ኃላፊነት እንዲወስድ የሚያስገድድ ረቂቅ መመርያ ተዘጋጀ

የጤና ሚኒስቴርን ፈቃድ አግኝተው በውጭ አገሮች የሕክምና አገልግሎት ተቋማት የሚታከሙ ኢትዮጵያውያን፣ የሕክምና አገልግሎት ጥራት ደረጃ ጉድለት፣ የሕክምና ስህተት ወይም የሙያ ግድፈት ቢፈጸምባቸው፣ የውጭ ሕክምና...

በአማራ ክልል የአሽከርካሪዎች ዕገታን መደበኛ የሥራ ቦታ አድርጎ የሚንቀሳቀሰው መበራከቱ ተገለጸ

በአማራ ክልል ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣው የአሽከርካሪዎች ዕገታ በአሁኑ ወቅት ክፍት የሥራ ቦታ እየሆነ መምጣቱ ተነገረ፡፡ አሽከርካሪዎችን በማገት ከፍተኛ ገንዘብ የሚጠይቁና ሲያዙም በአግባቡ በሕግ...

የባሕር ዳርና ድሬዳዋ ኤርፖርቶች የሲቪል በረራዎች ቁጥጥር ስርዓታቸውን አሳደጉ

በኢትዮጵያ ከሚገኙት አራት ዓለም አቀፍ ኤርፖርቶች መካከል የሆኑት የባህር ዳርና የድሬዳዋ ኤርፖርቶች፣ የአየር በረራዎች ቁጥጥር ክፍሎች ከጥር ወር 2017 ዓ.ም. ጀምሮ ማናቸውንም እስከ 25...

ኢትዮ ቴሌኮም አገልግሎቱን በርካሽ ዋጋ ማቅረቡ ከተወዳዳሪው ኩባንያ ቅሬታ እየቀረበበት መሆኑን አስታወቀ

ኢትዮጵያ ቴሌኮም ጉልህ የገበያ ድርሻ እያለው አገልግሎቱን በርካሽ ዋጋ ማቅረቡ ለተወዳዳሪው ኩባንያው ውድድሩን አስቸጋሪ ስላደረገበት፣ ‹‹መንግሥታዊ ኩባንያው ዋጋ እንዲጨምር መገደድ አለበት የሚል የቅሬታ ጥያቁ...

በአማራ ክልል በፀጥታ ችግር ምክንያት 39 ምድብ ችሎቶች ከአገልግሎት ውጪ መሆናቸው ተረጋገጠ

በስድስት ወራት 89 ዳኞች ሥራ መልቀቃቸው ተነግሯል የክልሉ ዳኞች ያለመከሰስ መብት ተጠበቀላቸው በአማራ ክልል በፀጥታ ችግር ምክንያት ከ221 ፍርድ ቤቶች 39 የዞንና የወረዳ ምድብ ችሎቶች አገልግሎት...

አዳዲስ ጽሁፎች

የጤናው ዘርፍ ባለፉት ስድሥት ወራት

የወባ በሽታ ከሰሃራ በታች በሚገኙ የአፍሪካ አገሮች ዋነኛ የጤናና የማኅበራዊ ቀውስ መንስዔ ነው፡፡ የዓለም ጤና ድርጅት እ.ኤ.አ. በ2024 ያወጣው መረጃም 263 ሚሊዮን ሰዎች የወባ...

የአዲስ አበባ የኮሪደር ልማት በባለሙያ ዓይን

(በጎ ጎኖችና እርምት የሚፈልጉ ጉዳዮች) በዮሐንስ መኮንን በጥር ወር 2016 ዓ.ም. የአዲስ አበባ ዋና ዋና ኮሪደሮችን በማዘመን ከተማዋን ለነዋሪዎቿና ለጎብኚዎቿ ምቹ ያደርጋታል የተባለ ፕሮጀክት በ43 ቢሊዮን...

በልዩነት ውስጥ ሆነንም እስኪ እንነጋገር

በገነት ዓለሙ ዴሞክራሲ መብቶችና ነፃነቶች የሚሠሩበት የሕዝብ አስተዳደር ነው፡፡ ሰብዓዊ መብቶችንና ነፃነቶችን መኗኗሪ ያደረገ ሥርዓት ነው፡፡ እነዚህ መሠረታዊ መብቶችና ነፃነቶች በተፈጥሮ የተገኙ፣ ሰው በመሆናችን ብቻ...

ለጤናማ የትራፊክ ፍሰትና ለመንገድ ደኅንነት ቅጣት መጣል ብቻውን መፍትሔ አይሆንም!

በአዲስ አበባ ከተማ ለተሽከርካሪዎች ምቹ የሆኑ መንገዶችን እየተመለከትን ነው፡፡ ከአዳዲሶቹ መንገዶች ባሻገር አንዳንድ ነባር መንገዶች የማስፋፊያ ሥራ ታክሎባቸው አገልግሎት ላይ ውለዋል፡፡ ከኮሪደር ልማቱ ጋር...

የግጭት አዙሪት ውስጥ ሆኖ የአፍሪካ ማዕከል መሆን ያዳግታል!

የአፍሪካ ኅብረት 38ኛው የመሪዎች ጉባዔ በአዲስ አበባ ሲካሄድ ብዙ ትዝ የሚሉ ጉዳዮች አሉ፡፡ እጅግ በጣም አሰልቺ፣ ውጣ ውረድ የበዛበትና ታላቅ ተጋድሎ ተደርጎበት ከከፍተኛ ዲፕሎማሲያዊ...

አገሬ ምንተባልሽ – ልብ ያለው ልብ ይበል

በቶማስ በቀለ ይቺ አገራችን ብዙ ተብሎላታልም፣ ብዙ ተወርቶባታልም፣ አገሪቱ በቅኝ ያልተገዛች ብቸኛ አገር (ላይቤሪያን ጨምሮ) ከመሆኗ አኳያ የሚነገርላት ብዙ ጥሩና የሚገርሙ ነገሮች ያሉትን ያህል፣ ከረሃብ...
[the_ad id="124766"]

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን