Thursday, November 30, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት በየመንና በጂቡቲ ችግር ውስጥ የነበሩ ኢትዮጵያውያን እንዲመለሱ አደረገ

ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት በየመንና በጂቡቲ ችግር ውስጥ የነበሩ ኢትዮጵያውያን እንዲመለሱ አደረገ

ቀን:

ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (አይኦኤም) በየመንና በጂቡቲ በችግር ላይ የነበሩ 146 ኢትዮጵያውያን ባለፈው ሳምንት መጀመሪያ ላይ ወደ አገራቸው እንዲመለሱ ማድረጉን አስታወቀ፡፡ ከተመለሱት ስደተኞች መካከል ሕፃናትም ጭምር የነበሩ ሲሆን፣ ተመላሾቹ የትራንስፖርት፣ መጠለያና ልብስ ያሉ ድጋፎች ተደርጎላቸው በመጨረሻ ወደየቀያቸው እንዲሄዱ መደረጉም ተጠቁሟል፡፡

ከተመላሾቹ መካከልም ከወላጆቻቸው የተለያዩ ሕፃናት ቤተሰቦችን የማፈላለግ ሥራም ከአዲስ አበባ የሴቶችና የሕፃናት ቢሮ እንዲሁም የተመድ ሕፃናት አድን ድርጅት ከሆነው ዩኒሴፍ ጋር በመተባበር እያከናወነ መሆኑን፣ ወላጆች እስኪገኙ ድረስ ግን ሕፃናቱ በአይኦኤም የሕፃናት ማቆያ እንዲሆኑ መደረጉ ተጠቁሟል፡፡

በሌላ በኩል የኢትዮ ኤርትራ ድንበርን አቋርጠው የገቡ 4500 ኤርትራውያን አስፈላጊው አፋጣኝ ዕርዳታ ተደርጎላቸው፣ ከሽሬ 20 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ወደሚገኘው የእንዳባጉና የስደተኞች መቀበያ ጣቢያ መሸኘታቸውን ድርጅቱ መጋቢት 7 ቀን 2009 ዓ.ም. አስታውቋል፡፡ ስደተኞቹ በጣቢያው በስደተኞችና ተመላሾች ጉዳይ አስተዳደር እንዲሁም የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የስደተኞች ኤጀንሲ በሆነው ዩኤንኤችሲአር የሚመዘገቡ ሲሆን፣ እንዳባጉና የስደተኞች ምዝገባ ጣቢያ በአሁኑ ወቅት በሦስት እጥፍ ከአቅሙ በላይ ስደተኞችን እያስተናገደ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡

የዩኤንኤችሲአር መረጃ እንደሚያመለክተው ወደ ጣቢያው ከገቡት አዲስ ስደተኞች 30 በመቶ የሚሆኑት ብቸኛ ሕፃናት (ወላጆቻቸው አብረዋቸው የሌሉ) ናቸው፡፡ 

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የመቃወም ነፃነት ውዝግብ በኢትዮጵያ

ስሟ እንዳይገለጽ የጠየቀችው በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ የሾላ አካባቢ...

የሲሚንቶን እጥረትና ችግር ታሪክ ለማድረግ የተጀመረው አጓጊ ጥረት

በኢትዮጵያ በገበያ ውስጥ ለዓመታት ከፍተኛ ተግዳሮት በመሆን ከሚጠቀሱ ምርቶች...

የብሔር ፖለቲካው ጡዘት የእርስ በርስ ግጭት እንዳያባብስ ጥንቃቄ ይደረግ

በያሲን ባህሩ በሪፖርተር የኅዳር 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ዕትም “እኔ...