Tuesday, October 3, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊለሦስት ቀናት ከፊል ጨለማ ውጧት የነበረችው ሞጆ ከተማ ሙሉ ኃይል አገኘች

ለሦስት ቀናት ከፊል ጨለማ ውጧት የነበረችው ሞጆ ከተማ ሙሉ ኃይል አገኘች

ቀን:

ከሁለት ማከፋፈያዎች የኤሌክትሪክ ኃይል የምታገኘው የበርካታ ኢንዱስትሪዎች መናኸሪያ ሞጆ ከተማ አንደኛው ማከፋፈያ በገጠመው ብልሽት ምክንያት ከየካቲት 11 እስከ 13 ቀን 2009 ዓ.ም. ድረስ በከፊል ጨለማ ውስጥ የቆየች ቢሆንም፣ መስመሩ ተስተካክሎ ሙሉ የኤሌክትሪክ ኃይል ማግኘቷ ተገለጸ፡፡

የኢንዱስትሪ ከተማ የሆነችው ሞጆ ከቆቃ ኃይል ማመንጫ ዘጠኝ ሜጋ ዋትና ስድስት ሜጋ ዋት ከሁለት ማከፋፈያዎች የኤሌክትሪክ ኃይል የምታገኝ ቢሆንም፣ ስድስት ሜጋ ዋት የሚያስተላልፈው ማሠራጫ ጣቢያ ብሬከር ተበላሽቶ ኃይል ተቋርጦ እንደነበር፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎት ዲስትሪቢዩሽን ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ብርሃኔ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

የኃይል አገልግሎት አቅርቦቱ በመቋረጡ መከላከያ፣ ኬብል ማምረቻ ፋብሪካ፣ ኢትዮ ጃፓን ጨርቃ ጨርቅ፣ ሞጆ ዘይት ፋብሪካ፣ ሞጆ ቆዳ ፋብሪካ፣ ሸዋ ታነሪ (ኢስት አፍሪካ ታነሪ ተብሏል)፣ ሞጆ ደረቅ ወደብ፣ ነዋሪዎች በከፊልና የተለያዩ ድርጅቶች ለሦስት ቀናት ችግር እንደገጠማቸው ተናግረዋል፡፡

ከቆቃ ቃይል ማመንጫ 45 ኪሎ ቮልት ያገኝ የነበረውና ስድስት ሜጋ ዋት የሚያስተላልፈው ጣቢያ ብሬከር በመበላሸቱ የተቋረጠውን ኃይል ለመመለስ የአቃቂ፣ የአዋሽ ሰባትና አዲስ አበባ ዲስትሪክቶች ተረባርበው እንደሠሩ አቶ መስፍን አስረድተዋል፡፡

በመሆኑም ሞጆ ከተማ ከየካቲት 13 ቀን 2009 ዓ.ም. ጀምሮ ሙሉ በሙሉ ኃይል እያገኘች መሆኗን ገልጸው፣ የኢንዱስትሪዎቹ ባለቤቶችም ሆኑ ነዋሪዎች ላሳዩት ትብብርና ትዕግሥት ምሥጋናቸውን አቅርበዋል፡፡  

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ተመድንና ዓለም አቀፋዊ ሕግን ከእነ አሜሪካ አድራጊ ፈጣሪነት እናድን!

በገነት ዓለሙ በእኔ የተማሪነት፣ የመጀመርያ ደረጃ ተማሪነት ጊዜ፣ የመዝሙር ትምህርት...

የሰላም ዕጦትና የኢኮኖሚው መንገራገጭ አንድምታ

በንጉሥ ወዳጅነው ፍራንክ ቲስትልዌይት የተባሉ አሜሪካዊ ጸሐፊ ‹‹The Great Experiment...

ድህነት የሀብት ዕጦት ሳይሆን ያለውን በአግባቡ ለመጠቀም አለመቻል ነው

በአንድነት ኃይሉ ድህነት ላይ አልተግባባንም፡፡ ብንግባባ ኖሮ ትናንትም ምክንያት ዛሬም...