Wednesday, February 12, 2025
- Advertisement -
- Advertisement -
ፍሬከናፍር​ ‹‹የታሪክ ተማሪዎቻችን ያለፈውን የኢትዮጵያ ታሪክ አሻራ ጠልቀው የሚመለከቱት፣ ሪቻርድ ፓንክረስት በከፈቱት...

​ ‹‹የታሪክ ተማሪዎቻችን ያለፈውን የኢትዮጵያ ታሪክ አሻራ ጠልቀው የሚመለከቱት፣ ሪቻርድ ፓንክረስት በከፈቱት መስኮት ነው፡፡››

ቀን:

spot_img

የቀድሞው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንትና የዩኔስኮ ለሰብአዊ መብትና ዴሞክራሲ ወንበር ፕሮፌሰር አንድርያስ እሸቴ፣ ለፕሮፌሰር ሪቻርድ ፓንክረስትና ሪታ ፓንክረስት መታሰቢያ በተዘጋጀ መጽሔት ላይ ካሰፈሩት ቀዳሚ ቃል የተወሰደ፡፡ ማክሰኞ የካቲት 14 ቀን 2009 ዓ.ም. ሥርዓተ ቀብራቸው የተፈጸመው ፕሮፌሰር ሪቻርድ ፓንክረስት ከባለቤታቸው ሪታ ጋር ላከናወኑት ዘርፈ ብዙ አገልግሎት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሕይወት እያሉ፣ በመሠረቱት ‹‹የኢትዮጵያ ጥናት መጽሔት-Journal of Ethiopian Studies›› በክብር ዘክሯቸዋል፡፡ ፕሮፌሰር አንድርያስ በቀዳሚ ቃላቸው ላይ የተንደረደሩት የፓንክረስት ቤተሰብን እንዲህ በመግለጽ ነው፡፡ ‹‹የፓንክረስት ስም በ20ኛው ክፍለ ዘመን በተለያዩ ዝግጅቶችና ሁነቶች በግንባር ቀደምትነት ተነስቷል፡፡ የሴቶች የመምረጥ መብት፣ የሠራተኛው መደብ መብት የማስከበርና የፀረ ፋሺስት ንቅናቄዎች፣ እንዲሁም በፀረ ቅኝ ግዛት ትግል ስሙ ይታወሳል፡፡ ወደ ኢትዮጵያም ስንመጣ የፓንክረስት ቤተሰብ [እናት ሲልቪያ፣ ልጅ ሪቻርድና የልጅ ሚስት ሪታ] ኢትዮጵያ በፋሺስት ኢጣሊያ ላይ በነበራት አይበገሬነት ተሳትፏል፡፡ ድኅረ ጦርነትም ኢትዮጵያና ኤርትራ አብረው እንዲሆኑ ብዙ ጥሯል፡፡››

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የሃዋሳ ሐይቅ ዳርቻው ሩጫ

ዓመታዊው የሃዋሳ ሐይቅ ዳርቻ የግማሽ ማራቶንና በተለያየ ዕድሜ ክልል...

‹‹አሻም አዲ››

“አሻም አዲ! አሻም አዲ! አሻም አዲ!..." አዲ የጎረቤታችን አዛውንት...

አታልቅስ አትበሉኝ

 አታልቅስ በሉኝ  ግዴለም ከልክሉኝ፣  የፊቴን ፀዳል  አጠልሹት በከሰል ፣  የግንባሬን ቆዳ  ስፉት በመደዳ፣  ጨጓራ አስመስሉት።              ...

የኢትዮጵያ ስፖርት አካዴሚ ጉዞን የቃኘው የአርባ ምንጩ መድረክ

በቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ትዕዛዝ እንዲገነባ የሆነው፣ ቀደም...