Sunday, September 24, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ፍሬከናፍር​ ‹‹የታሪክ ተማሪዎቻችን ያለፈውን የኢትዮጵያ ታሪክ አሻራ ጠልቀው የሚመለከቱት፣ ሪቻርድ ፓንክረስት በከፈቱት...

​ ‹‹የታሪክ ተማሪዎቻችን ያለፈውን የኢትዮጵያ ታሪክ አሻራ ጠልቀው የሚመለከቱት፣ ሪቻርድ ፓንክረስት በከፈቱት መስኮት ነው፡፡››

ቀን:

የቀድሞው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንትና የዩኔስኮ ለሰብአዊ መብትና ዴሞክራሲ ወንበር ፕሮፌሰር አንድርያስ እሸቴ፣ ለፕሮፌሰር ሪቻርድ ፓንክረስትና ሪታ ፓንክረስት መታሰቢያ በተዘጋጀ መጽሔት ላይ ካሰፈሩት ቀዳሚ ቃል የተወሰደ፡፡ ማክሰኞ የካቲት 14 ቀን 2009 ዓ.ም. ሥርዓተ ቀብራቸው የተፈጸመው ፕሮፌሰር ሪቻርድ ፓንክረስት ከባለቤታቸው ሪታ ጋር ላከናወኑት ዘርፈ ብዙ አገልግሎት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሕይወት እያሉ፣ በመሠረቱት ‹‹የኢትዮጵያ ጥናት መጽሔት-Journal of Ethiopian Studies›› በክብር ዘክሯቸዋል፡፡ ፕሮፌሰር አንድርያስ በቀዳሚ ቃላቸው ላይ የተንደረደሩት የፓንክረስት ቤተሰብን እንዲህ በመግለጽ ነው፡፡ ‹‹የፓንክረስት ስም በ20ኛው ክፍለ ዘመን በተለያዩ ዝግጅቶችና ሁነቶች በግንባር ቀደምትነት ተነስቷል፡፡ የሴቶች የመምረጥ መብት፣ የሠራተኛው መደብ መብት የማስከበርና የፀረ ፋሺስት ንቅናቄዎች፣ እንዲሁም በፀረ ቅኝ ግዛት ትግል ስሙ ይታወሳል፡፡ ወደ ኢትዮጵያም ስንመጣ የፓንክረስት ቤተሰብ [እናት ሲልቪያ፣ ልጅ ሪቻርድና የልጅ ሚስት ሪታ] ኢትዮጵያ በፋሺስት ኢጣሊያ ላይ በነበራት አይበገሬነት ተሳትፏል፡፡ ድኅረ ጦርነትም ኢትዮጵያና ኤርትራ አብረው እንዲሆኑ ብዙ ጥሯል፡፡››

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የቤት ባለንብረቶች የሚከፍሉትን ዓመታዊ የንብረት ታክስ የሚተምን ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጀ

በአዋጁ መሥፈርት መሠረት የክልልና የከተማ አስተዳደሮች የንብረት ታክስ መጠን...

እንደ ንብረት ታክስ ያሉ ወጪን የሚያስከትሉ አዋጆች ከማኅበረሰብ ጋር ምክክርን ይሻሉ!

የመንግሥትን ገቢ በማሳደግ ረገድ አስተዋጽኦ እንዳላቸው የሚታመኑት የተጨማሪ እሴት...

ለዓለምም ለኢትዮጵያም ሰላም እንታገል

በበቀለ ሹሜ ያለፉት ሁለት የዓለም ጦርነቶች በአያሌው የኃያል ነን ባይ...