የቀድሞው የፖሊሲ ጥናትና ምርምር ማዕከል ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ በረከት ስምዖን፣ በጎንደር ከተማ በቅርቡ በተደረገው የአማራና የትግራይ የሕዝብ ለሕዝብ መድረክ ላይ የተናገሩት፡፡ አቶ በረከት በዲስኩራቸው ምሁራን በውጪ ያሉት ኢትዮጵያውያን ጭምር፣ ‹‹በመድረኩ ማሳተፍ አለብን›› ብለው የተንደረደሩት ‹‹ከዚህ ከደረስንበት ወደሚቀጥለው እንዴት ነው የምንሄደው ብለን አሳታፊ በሆነ መንገድ መመለስ አለበት›› በማለትም ነው፡፡ በቅርቡ ከመንግሥታዊ ሥልጣናቸው በፈቃዳቸው የለቀቁት አቶ በረከት፣ መንግሥት ለውጦችን አጠናክሮ መቀጠል እንደሚኖርበት፣ የተመዘገቡ ለውጦች ላይ የሚሰነዘሩ ጥቃቶችን ማስቆም አለበት ብለዋል፡፡ ‹‹ፖሊሲዎች ላይ የሚሰነዘሩትን ያልተገቡ ተፅዕኖዎችን መቋቋም የሚችል መንግሥት መሆን አለበት፡፡ በዚህ ደረጃ ብዙ ችግሮች ናቸው ያሉት፤›› በማለትም አስረግጠው ተናግረዋል፡፡