Friday, March 24, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

ክቡር ሚኒስትር

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሚስታቸው ጋር እያወሩ ነው]

  • ምነው ተከዝሽ?
  • ብዙ ነገር ያሳስበኛል፡፡
  • ምን ያሳስብሻል?
  • የወደፊት ሕይወታችን፡፡
  • የወደፊት ሕይወታችን ምን ሆነ?
  • መቼ ይገባሃል አንተ?
  • ማለት?
  • ቤት እንኳን መቼ አለን?
  • ይኼኛው ቤትስ?
  • አይ አንተ?
  • ምነው?
  • ቤቱ እኮ የመንግሥት ነው፡፡
  • ቢሆንስ እየኖርንበት አይደለ እንዴ?
  • ዕድሜ ልክህን ሥልጣን ላይ የምትቆይ ይመስልሃል?
  • የሰማሽው ነገር አለ እንዴ?
  • ምን?
  • ከሥልጣን ልነሳ ነው እንዴ?
  • ኧረ የሰይጣን ጆሮ ይደፈን፡፡
  • ታዲያ ምንድን ነው የምታወሪው?
  • ስለወደፊቱ ዕጣ ፈንታ ከአሁኑ ማሰብ አለብህ፡፡
  • እና ምን ይደረግ እያልሽ ነው?
  • ከአንድ ሰው ጋር ሳወራ ነበር፡፡
  • እሺ፡፡
  • እነዚህ የ40/60 ቤቶች በጣም አሪፍ ናቸው አሉ፡፡
  • እሱማ እኔም ሰምቻለሁ፡፡
  • ታዲያ እነሱ ቤቶች እንዴት ናቸው?
  • ምን እያልሽ ነው?
  • የምለውማ ገብቶሃል፡፡
  • ሴትዮ ጤነኛ ነሽ ግን?
  • በሚገባ እንጂ፡፡
  • እነሱ እኮ የሕዝብ ናቸው፡፡
  • አይ አንተ?
  • ስሚ ሕዝብ ቆጥቦ እኮ ነው የተሠሩት፡፡
  • ቢሆንም እኔ ወሬ ሰምቻለሁ፡፡
  • የምን ወሬ?
  • የተዘጋጁት ለማን እንደሆነ፡፡
  • ለማን ነው?
  • ለባለሥልጣናት!

[ክቡር ሚኒስትሩ አንድ ወዳጃቸው ሚኒስትር ጋ ደወሉ] 

  • ሄሎ ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • እንዴት ነህ ወዳጄ?
  • ሰላም ነው ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ቢዚ እንደሆንክ አውቃለሁ፣ አንድ ነገር ልጠይቅህ ነበር፡፡
  • ምን ክቡር ሚኒስትር?
  • እነዚህ 40/60 ቤቶች እንዴት ናቸው?
  • ያው በጥሩ ሁኔታ እየተሠሩ ነው፡፡
  • እሱማ አውቃለሁ ግን…
  • ግን ምን ክቡር ሚኒስትር?
  • ቤቶቹን እንዴት ማግኘት ይቻላል?
  • ተመዝግበዋል እንዴ ክቡር ሚኒስትር?
  • ኧረ በፍጹም፡፡
  • እና ቤቶቹን ወደዷቸው?
  • በጣም ነው የወደድኳቸው፡፡
  • ዋናው እንኳን እርስዎ ወደዷቸው፡፡
  • ማግኘት እችላለሁ እንዴ?
  • እንዴታ ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • የተሠሩት ለሕዝቡ መስሎኝ?
  • የተሠሩትማ…
  • እ…
  • ለእኛው ነው!

[የክቡር ሚኒስትሩ የቅርብ ዘመድ ደወለላቸው] 

  • ሄሎ ጋሼ፡፡
  • እሺ እንዴት ነህ?
  • ኧረ ችግር ውስጥ ነኝ ጋሼ፡፡
  • የምን ችግር ደግሞ?
  • ትንሽ ከመንግሥት ጋር እየተጋጨሁ ነው፡፡
  • ተቃዋሚ ሆንኩ እንዳትለኝ?
  • እንደሱ አይደለም ጋሼ፡፡
  • ታዲያ ምን ተፈጠረ?
  • በታክስ ጉዳይ ነው፡፡
  • ታክስ አትከፍልም እንዴ?
  • ኧረ እኔ እከፍላለሁ፡፡
  • በታክስ እኔ ቀልድ እንደማላውቅ ታውቃለህ?
  • አውቃለሁ ጋሼ፡፡
  • ታዲያ ምንድን ነው?
  • አንድ ከገጠር ያመጣሁት ዘመዳችን ነበር፡፡
  • እሺ ምን ሆነ?
  • ለእሱ የከፈትኩለት ሱቅ ነበር፡፡
  • እሺ፡፡
  • እኔ ሳላውቅ ለካ ለዓመታት ታክስ ከፍሎ አያውቅም፡፡
  • ታዲያ አንተ ምን አገባህ?
  • ሱቁ በእኔ ስም ነው ያለው፡፡
  • ወይ ጣጣ፡፡
  • አሁን ዓቃቤ ሕግ ነገሩን እያከረረው ነው፡፡
  • እና ምን አድርግ ነው የምትለኝ?
  • አንተ ሚኒስትር አይደለህ እንዴ ጋሼ?
  • ታዲያ ብሆንስ?
  • ክሱን አስቋርጠው፡፡
  • እስቲ ለማንኛውም የዳኛውን ስምና ቁጥር ቴክስት አድርግልኝ፡፡
  • እሺ ጋሼ፡፡

[ክቡር ሚኒስትሩ ዳኛው ጋ ደወሉ] 

  • ሄሎ፡፡
  • እንዴት ነህ ክቡር ዳኛ?
  • ማን ልበል?
  • ክቡር ሚኒስትር ነኝ፡፡
  • እንዴት ነዎት ክቡር ሚኒስትር?
  • ሰላም ነኝ፡፡
  • ምን ልርዳዎት?
  • አንድ ዘመዴ አንተ ጋ ኬዝ ነበረው፡፡
  • የምን ኬዝ?
  • ትናንትና በታክስ ጉዳይ ፍርድ ቤት የነበረው ኬዝ፡፡
  • እ… አወቅኩት ሰውዬውን፡፡
  • ስለእሱ ጉዳይ ለማውራት ነበር፡፡
  • ያውሩኛ ምን ችግር አለው?
  • በስልክ ጥሩ ስላልሆነ በአካል ተገናኝተን ብናወራስ?
  • ክቡር ሚኒስትር ሥራ ስለሚበዛብኝ ከቻሉ የሚፈልጉትን በስልክ ይንገሩኝ፡፡
  • ሰውዬው ጥፋተኛ አይደለም፡፡
  • እሱማ በፍርድ ቤት የሚታይ ጉዳይ ነው፡፡
  • አይገባህም እንዴ አንተ?
  • ስልኩን ልዘጋው ነው ክቡር ሚኒስትር?
  • በጣም ተናንቀናል ማለት ነው፡፡
  • ምን አሉኝ?
  • የምነግርህን አትሰማም እንዴ?
  • ክቡር ሚኒስትር ፍርድ ቤቱ በትዕዛዝ አይደለም የሚሠራው፡፡
  • እና በምንድን ነው የሚሠራው?
  • እንዴት እንደሚሠራ ለማወቅ ሕገ መንግሥቱን ቢያነቡት ጥሩ ነው፡፡
  • እና ትዕዛዙን አትቀበልም?
  • ለመሆኑ ሰሞኑን ሚዲያ ተከታትለዋል?
  • በምን ጉዳይ ላይ?
  • አሜሪካ ስለተፈጸመው ጉዳይ፡፡
  • ምን ተፈጸመ?
  • ፕሬዚዳንቱ አንድ ትዕዛዝ አውጥተው ነበር፡፡
  • እሺ፡፡
  • ከዛ በኋላ ግን የፕሬዚዳንቱን ትዕዛዝ ፍርድ ቤት ሻረው፡፡
  • ምን እያልከኝ ነው?
  • ልልዎት የፈለኩትማ ፍርድ ቤትን ማንም አያዘውም ነው፡፡
  • ማሞ ሌላ መታወቂያው ሌላ አሉ፡፡
  • እንዴት ክቡር ሚኒስትር?
  • አሜሪካ ሌላ…
  • እ…
  • ኢትዮጵያ ሌላ!

[ክቡር ሚኒስትሩ ከአማካሪያቸው ጋር እያወሩ ነው] 

  • ስማ ይኼ ትራምፕ የሚባለውን ሰውዬ እየተከታተልከው ነው?
  • በሚገባ ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ያወጣውን መመርያ ሰምተሃል አይደል?
  • ትራቭል ባኑን ነው?
  • ታዲያስ?
  • እሱ እኮ እኛን አይመለከትም፡፡
  • እንዴት አይመለከትም?
  • ለሰባት አገሮች ነው እኮ የወጣው፡፡
  • እኔ እሱን አይደለም የምልህ፡፡
  • ታዲያ ምን እያሉኝ ነው?
  • እዛ ያሉ ኢትዮጵያውያንን ጠራርጎ ሊልካቸው ነው፡፡
  • ማለት?
  • በቃ ይኼ ዶክመንት የሌለው ሁሉ መጠረዙ አይቀርም፡፡
  • ኧረ እንደዛ የሚባል ነገር የለም፡፡
  • ሰውዬው ሕገወጥ ስደተኛን አባርራለሁ ብሏል፡፡
  • ቢሆንም due process የሚባል ነገር አለ፡፡
  • ምንድን ነው እሱ?
  • አሜሪካ ምድር የረገጠ ሰው ዝም ብሎ አይባረርም፡፡
  • እንዴት አይባረርም?
  • ኬዙ በፍርድ ቤት ተይዞ እስከ አሥር ዓመት ሊቆይ ይችላል፡፡
  • ሰውዬው ለምን እንደተመረጠ ታውቃለህ?
  • ለምንድን ነው?
  • የማስፈጸም ብቃቱ ፈጣን በመሆኑ ነው፡፡
  • ምን እያሉ ነው ታዲያ?
  • አዲስ ስትራቴጂ ነው የሚጠቀመው፡፡
  • ምን ዓይነት ስትራቴጂ?
  • Fast due process የሚሉት፡፡
  • ስለ due process አላውቅም ብለውኝ አልነበር እንዴ?
  • የምትለውን ልስማ ብዬ ነው እንጂ በደንብ ነው ጠንቅቄ የማውቀው፡፡
  • እኔ ግን አሁን ስለሚሉት ነገር ሰምቼም አላውቅም፡፡
  • አታነብማ ችግሩ እሱ ነው፡፡
  • ብለው ነው ክቡር ሚኒስትር?
  • ለማንኛውም አሁን መዘጋጀት አለብን፡፡
  • ለምኑ ነው የምንዘጋጀው?
  • አሁን የመንግሥትን ልማት ሲያንቋሽሹ የነበሩ ጠላቶቻችን መምጫቸው ቀርቧል፡፡
  • እ…
  • በቃ በየጊዜው ባለሥልጣናትን ሲያዋርዱ የነበሩ ጉዳቸው ነው፡፡
  • አልገባኝም ክቡር ሚኒስትር?
  • ስማ ያ ሰውዬ ጠርዞ ሲልካቸው እዚህ በሚገባ እንቀበላቸዋለን፡፡
  • ሰሞኑን ግን መንግሥት መግለጫ አውጥቷል፡፡
  • ምን የሚል?
  • እዛ ያሉ ኢትዮጵያውያን መንግሥትን የሚቃወሙት ለግሪን ካርድ ስለሆነ ወደ አገራቸው ተመልሰው በልማት ላይ መሳተፍ ይችላሉ ብሏል፡፡
  • እሱማ የሚሰማሩት ልማት ላይ ነው፡፡
  • ታዲያ እርስዎ ምን እያሉ ነው?
  • ጥያቄው የሚያለሙት ምንድን ነው የሚለው ነው?
  • ምንድን ነው የሚያለሙት ታዲያ?
  • ቂሊንጦን!

 

 

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

አሜሪካ ሕወሓትን በማሳመንና በመጫን በሰላም ሒደቱ ትልቅ ሚና መጫወቷን የኢትዮጵያ ዋና ተደራዳሪ አስታወቁ

የተመድና የአውሮፓ ኅብረት አበርክቶ አሉታዊ እንደነበር ጠቁመዋል በመንግሥትና በሕወሓት መካከል...

አገር የሚገቡ የግል ዕቃዎችን በሚገድበው መመርያ ምክንያት በርካታ ንብረቶች በጉምሩክ መያዛቸው ተገለጸ

በአየር መንገድ ተጓዦች ወደ አገር የሚገቡትን የግል መገልገያ ዕቃዎች...

ብሔራዊ ባንክ ለጥቃቅንና አነስተኛ ብድሮች ዋስትና መስጠት ሊጀምር ነው

ኢንተርፕራይዞችን ብቻ የሚያገለግል የፋይናንስ ማዕከል ሥራ ጀመረ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ...

አዋሽ ባንክ ለሁሉም ኅብረተሰብ የብድር አገልግሎት የሚያስገኙ ሁለት ክሬዲት ካርዶች ይፋ አደረገ

አዋሽ ባንክ ለሁሉም የኅብረተሰብ ክፍሎች በዘመናዊ መንገድ ብድር ማስገኘት...
- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

ጠቅላይ ሚንስትር ዓብይ አቶ ጌታቸው ረዳን የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር አድርገው ሾሙ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ(ዶ/ር) አቶ ጌታቸው ረዳ የትግራይ ክልል...

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሚያከብሯቸው አንድ የቀድሞ ጉምቱ ፖለቲከኛ ስልክ ተደውሎላቸው እያወሩ ነው]

አንዳንድ ነገሮች ቢያሳስቡኝ ነው ቀጠሮ ሳልይዝ ላወራህ የፈለኩት ክቡር...

የትግራይ ክልል የሽግግር አስተዳደር ምሥረታና የሰላም ስምምነቱ ሒደት

በትግራይ ክልል ጊዜያዊ የሽግግር መንግሥት ለመመሥረት ደፋ ቀና እየተባለ...

ጥራዝ ነጠቅነት!

ከሜክሲኮ ወደ ጀሞ እየሄድን ነው፡፡ የተሳፈርንበት አሮጌ ሚኒባስ ታክሲ...

አወዛጋቢነቱ የቀጠለው የአዲስ አበባ የጤፍ ገበያ

ሰሞኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በጤፍ የተከሰተውን የዋጋ ንረት...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሚያከብሯቸው አንድ የቀድሞ ጉምቱ ፖለቲከኛ ስልክ ተደውሎላቸው እያወሩ ነው]

አንዳንድ ነገሮች ቢያሳስቡኝ ነው ቀጠሮ ሳልይዝ ላወራህ የፈለኩት ክቡር ሚኒስትር? እርሶዎማ ቀጠሮ መያዝ አያስፈልግዎትም። ምን ገጠመዎት? እኔማ ምን ይገጥመኛል፣ አንተኑ ልጠይቅህ እንጂ? ምን? እውነት ለመናገር የማየው ነገር አሳስቦኛል። ይንገሩኝ...

[የባለሥልጣኑ ኃላፊ የቴሌኮም ኩባንያዎች የስልክ ቀፎ የመሸጥ ፈቃድ እንዳላቸው ለማረጋገጥ ክቡር ሚኒስትሩ ጋር ደወሉ]

ክቡር ሚኒስትር ዕርምጃ ከመውሰዳችን በፊት አንድ ነገር ለማጣራት ብዬ ነው የደወልኩት። እሺ ምንን በተመለከተ ነው? የቴሌኮም ኩባንያዎችን በተመለከተ ነው። የቴሌኮም ኩባንያዎች ምን? የቴሌኮም ኩባንያዎች የሞባይል ቀፎ እንዲሸጡ በሕግ...

[ክቡር ሚኒስትሩ ተቋቋመ ስለተባለው የሽግግር መንግሥት ከአማካሪያቸው መረጃ እየጠየቁ ነው]

እኛ ሳንፈቅድ እንዴት ሊያቋቁሙ ቻሉ? ስምምነታችን እንደዚያ ነው እንዴ? በስምምነታችን መሠረትማ እኛ ሳንፈቅድ መቋቋም አይችልም። የእኛ ተወካዮችም በአባልነት መካተት አለባቸው። ታዲያ ምን እያደረገ ነው? ስምምነቱን መጣሳቸው...