Monday, May 29, 2023
- ማስታወቂያ -
- ማስታወቂያ -

ምርት ገበያ ከ10 ቢሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያላቸው ምርቶችን በኤሌክትሮኒክ ግብይት ማስተናገዱን አስታወቀ

- ማስታወቂያ -

ተዛማጅ ፅሁፎች

– በክልሎች ሰባት የግብይት ማዕከላትን እንደሚከፍት ገልጿል

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ ከሰባት ዓይነት የግብርና ምርቶች ግብይት 10 ቢሊዮን 108 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ ግብይት ማከናወኑን አስታወቀ፡፡ በመንፈቅ ዓመቱ ከ246,652 ሜትሪክ ቶን ምርት አገበያይቷል፡፡

የምርት ገበያው ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ኤርሚያስ እሸቱ ዓርብ ጥር 12 ቀን 2009 ዓ.ም. በጽሕፈት ቤታቸው በሰጡት መግለጫ እንዳሉት፣ በስድስት ወራት ውስጥ የተከናወኑት ግብይቶች 89 በመቶው በኤሌክትሮኒክ ዘዴ መካሄዳቸውን፣ የተቀሩት ግን እንደ ቀድሞው ድምፅን በማስተጋባት በግብይት መድረኩ ተካሂደዋል፡፡

በስድስቱ ወራት ውስጥ የተካሄደው ግብይት በምርት መጠን ሲታይ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት አኳያ የስድስት ከመቶ ቅናሽ ቢያሳይም፣ የምርት ገበያውን ዕቅድ 96 በመቶ ያሳካ እንደነበር ዋና ሥራ አስፈጻሚው ገልጸዋል፡፡ በምርት ዋጋ በኩልም የዕቅዱን 94 ከመቶ እንደተገበረ ተገልጿል፡፡

ምርት ገበያው ቡና፣ ሰሊጥ፣ ነጭ ቦሎቄ፣ ቀይ ቦሎቄ፣ በቆሎ፣ ማሾና ስንዴ በማገበያየት ላይ ሲሆን፣ ካገበያያቸው ከእነዚህ ምርቶች ውስጥ የቡና 15 በመቶ እንዲሁም የነጭ ቦሎቄ ግብይት መጠን በ23 በመቶ ጭማሪ ማሳየቱን አቶ ኤርሚያስ አብራርተዋል፡፡ በግብይት ዋጋ ረገድ ካለፈው ተመሳሳይ ወቅት አኳያ የ19 በመቶ ጭማሪ ከመገኘቱ ባሻገር የቡና ግብይት 35 በመቶ እንዲሁም የነጭ ቦሎቄ ግብይት በ82 በመቶ ዕድገት ማሳየታቸውም ተጠቅሷል፡፡

በስድስት ወራት ውስጥ የተገኘው ውጤት ባለፉት 18 ወራት ውስጥ ሲተገበር ከቆየው የኤሌክትሮኒክ ግብይት ዘዴ አኳያ አመርቂና ዕድገቱም ጤናማ የሚባል ነው ያሉት አቶ አርሚያስ፣ ምርት ገበያው ገዥና ሻጭ በድምፅ እያስተጋቡ የሚገበያዩበት አሠራር ቀስ በቀስ እየቀረ እንደሚመጣ ተናግረዋል፡፡

ተወያዮች ድምፅ እያወጡ በማስተጋባት የሚያካሂዱት ግብይት በርካታ ግድፈቶች፣ ሆን ተብሎም ሆነ በስህተት የሚፈጸሙ የግብይት ሕግ ጥሰቶች ሲስተናገዱበት መቆየቱን የገለጹት አቶ ኤርሚያስ፣ አዲሱ በኮምፒዩተር የተደገፈ የኤሌክትሮኒክ ግብይት ግን በተገበያዮች መካከል ምንም ዓይነት ንክኪ እንዳይኖር ከማድረግ ባሻገር፣ ገዥና ሻጭ እነማን እንደሆኑ የማታወቅበት አሠራር በመሆኑ የግብይት ተዓሚነትን ይበልጥ እንደሚያሰፍን ገልጸዋል፡፡

በአዲስ አበባ ልደታ አካባቢ አልሳም ጨለለቅ ሕንፃ ላይ የሚገኘው የምርት ገበያው ብቸኛ የግብይት መድረክ ነው፡፡ በሦስት ወራት ውስጥ በሐዋሳ፣ በነቀምት እንዲሁም በሑመራ የኤሌክትሮኒክ ግብይት ማዕከሎች እንደሚከፈቱ ያስታወቁት አቶ ኤርሚያስ፣ ከሦስቱ በተጨማሪ በጂማ፣ በአዳማ፣ በጎንደርና በኮምቦልቻም ተመሳሳይ የግብይት ማዕከሎች ይፋ እንደሚደረጉና ለገበሬው በቅርብ ሆነው ግብይት ለማካሄድ እንዲቻል እንደሚያግዙ ይጠበቃል ብለዋል፡፡

በየቀኑ ከ200 ሚሊዮን ብር ያላነሰ ግብይት እንደሚፈጽም ያስታወሱት አቶ ኤርሚያስ፣ በግብይት ሒደቱ ምንም ዓይነት የውል ጥሰት ችግሮች ሳያስመዘግብ እንደዘለቀ ጠቅሰው፣ ይሁንና በኮንትሮባንድና በመሰል ችግሮች ምክንያት ወደ ምርት ገበያው መግባት ያለባቸው ምርቶች እንዳይገቡ ጫና እያሳደረ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ የስትራቴጂ ኦፊሰር የሆኑት አቶ ኃይለ ሚካኤል ኃይሌም በኮንትሮባንድ ምክንያት ቀይ ቦሎቄና ማሾ ወደ ምርት ገበያው መምጣት በሚገባቸው መጠን ልክ እየገቡ እንዳልሆነ ገልጸዋል፡፡

በአገር ውስጥና በውጭ ገበያዎች መካከል ያለውን የዋጋ ልዩነት ለማጥበብ በማሰብ ሲሠራበት የነበረውና ከአራት ዓመታት በፊት የተቋረጠው አሠራር በቡና ላይ በድጋሚ ሊተገበር እንደሚችል አቶ ኤርሚያስ፣ እንዲሁም የምርት ገበያው የኦፕሬሽን ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ አቶ በኃይሉ ንጉሤ ተናግረዋል፡፡

የመጋዘን አሠራር ከምርት ገበያው ውጭ ከተደረገ በኋላ በመጣው አዲስ አሠራር በርካታ ለውጦች መመዝገባቸውን አቶ ኤርሚያስ ቢገልጹም በምርት ጥራት፣ በጉቦ የምርት ደረጃን ከፍና ዝቅ ለማስደረግ ከቡና ቀማሾች ጋር መደራደር፣ ወዘተ. ያሉት ችግሮች በምርት ገበያው ላይ የሚቀርቡ ስሞታዎች እንደሆኑ በመጥቀስ ጋዜጠኞች ጥያቄ አቅርበዋል፡፡ ከዚህም በላይ ምርት ገበያው ለዓመታት በጥቂት ምርቶች ላይ ብቻ ተወስኖ መቆየቱ ለምን እንዳልተለወጠና አጠቃላይ እያሳየ ያለው እንቅስቃሴ ላይ ዕድገት ይታይበት እንደሆነ ጥያቄዎች ለምርት ገበያው ኃላፊዎች ከቀረቡት ውስጥ ይጠቀሳሉ፡፡

ባለፈው ዓመት በምርት መጠንና በዋጋ በኩል ምርት ገበያው ከፍተኛ የተባለውን ግብይት ማከናወኑን ያስታወሱት አቶ ኤርሚያስ፣ 632 ሺሕ ሜትሪክ ቶን ምርቶች ተገበያይተው ከ23 ቢሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያላቸው ግብይቶች መፈጸማቸው የምርት ገበያውን ጤናማ የዕድገት ጉዞ እንደሚያመላክቱ አስረድተዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በምርት ጥራት ቁጥጥር፣ በቡና እርጥበትና በመሳሰሉት ላይ ቁጥጥር እንደሚያደርግ አብራርተው፣ በቡና ቀመሳ ወቅት በተለይ ቡናው የማን እንደሆነ በማይታወቅበት አሠራር ደረጃ እንደሚወጣ፣ የሚቀርቡ ስሞታዎችም ከእውነታው የራቁ ናቸው በማለት አጣጥለዋቸዋል፡፡ ማጥጥርከማደክቱ

spot_img
- Advertisement -spot_img

የ ጋዜጠኛው ሌሎች ፅሁፎች

- ማስታወቂያ -

በብዛት ከተነበቡ ፅሁፎች