Friday, September 22, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናደቡብ ሱዳን ኢትዮጵያን የሚጎዳ ስምምነት ከግብፅ ጋር አለመፈጸሟን አስታወቀች

ደቡብ ሱዳን ኢትዮጵያን የሚጎዳ ስምምነት ከግብፅ ጋር አለመፈጸሟን አስታወቀች

ቀን:

ደቡብ ሱዳን ሰሞኑን ከግብፅ ጋር ባደረገችው የሁለትዮሽ ግንኙነት፣ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን የሚጎዳ የሴራ ስምምነት ፈጽማለች ተብሎ የሚናፈሰው መረጃ ሐሰት መሆኑን ገለጸች፡፡

በኢትዮጵያ የደቡብ ሱዳን አምባሳደር ጀምስ ፒታ ሞርጋ ሰሞኑን በሰጡት መግለጫ፣ የደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት በግብፅ ያደረጉት ጉብኝት የተለመደው የሁለትዮሽ የወዳጅነት ግንኙነት መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የደቡብ ሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ልዩ ረዳት አተም ደንግ ዋለዋለ በበኩላቸው፣ ‹‹በደቡብ ሱዳን የውጭ ግንኙነት ላይ ማንም ሊያዝ አይችልም፤›› ብለዋል፡፡

የተለያዩ የውጭ ሚዲያዎች በስም ያልተጠቀሱ የደቡብ ሱዳን ከፍተኛ ባለሥልጣንን እንደ ምንጭ በመጠቀም ባወጡት ዘገባ፣ የግብፅ ፕሬዚዳንት አብዱልፈታህ አልሲሲ ከደቡብ ሱዳን አቻቸው ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ጋር በካይሮ ተገናኝተው ‹‹‹አግባብ ያልሆነ ስምምነት›› መፈጸማቸውን ገልጸዋል፡፡

በዚህ ስምምነት ግብፅ በደቡብ ሱዳን በኩል የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ላይ አደጋ መጣል እንድትችል፣ እንዲሁም የኢትዮጵያ ውስጣዊ ፖለቲካ እንዳይረጋጋ ለማድረግ መስማማታቸውን ዘግበዋል፡፡

በኢትዮጵያ የደቡብ ሱዳን አምባሳደር በሰጡት ቃለ ምልልስ ግን ይኼንን ዘገባ መሠረተ ቢስ ብለውታል፡፡

ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ባለፈው ሳምንት ግብፅን ሲጎበኙ በይፋ በወጣው መረጃ መሠረት፣ ግብፅ የደቡብ ሱዳን መንግሥትን በተለያዩ ዘርፎች ለመርዳትና ወቅታዊ የደቡብ ሱዳን ቀውስን ለመፍታት እንደምትሠራ አሳውቃለች፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ከሳምንት በፊት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽ፣ ደቡብ ሱዳን ለኢትዮጵም ሆነ ኢትዮጵያ ለምትገኝበት ቀጣና ፈተና መሆኗን መግለጻቸው ይታወሳል፡፡

በኢትዮጵያ አደራዳሪነት በደቡብ ሱዳን መንግሥትና በተቃዋሚዎቹ መካከል የሰላም ስምምነት የተደረሰ ቢሆንም፣ ይህንን ስምምነት ተግባራዊ ለማድረግ አልተቻለም፡፡ ለዚህ በምክንያትነት ከሚጠቀሱት ችግሮች መካከል የኢጋድ አባል አገሮችም ሆኑ ሌሎች ዓለም አቀፍ ተዋናዮች የተለያየ አቋም መያዛቸው መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጠቁመዋል፡፡

ይህንን ችግር ለመፍታትም በአዲስ አበባ ከሚካሄደው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ ጎን ለጎን፣ ዓለም አቀፍ ጉባዔ በደቡብ ሱዳን ሁኔታ ላይ እንደሚካሄድ አስረድተዋል፡፡  

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ባለሙያዎች ኮሚሽን ሪፖርት ምን ይዟል?

ለአሜሪካ ድምፅ አማርኛ ዝግጅት የስልክ አስተያየት የሰጡ አንድ የደንበጫ...

መንግሥት በአማራ ክልል ለወደሙ የአበባ እርሻዎች ድጋፍ እንዲያደርግ ተጠየቀ

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአማራ ክልል የተፈጠረው ግጭትና አለመረጋጋት በቢዝነስ...

አምናና ዘንድሮ!

እነሆ መስከረም ጠብቶ በአዲስ መንፈስ ተሞልተን መንገድ ጀምረናል። ‹‹አዲስ...