Wednesday, September 27, 2023
- ማስታወቂያ -
- ማስታወቂያ -

በኢትዮጵያና በታንዛኒያ መንግሥታት መካከል ሲካሄድ የቆየው የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ስምምነት ድርድር ተጠናቆ፣ ከረቡዕ ጥር 10 ቀን 2009 ዓ.ም. ጀምሮ በታንዛኒያ አሩሻ ከተማ ሲካሄድ ከቆየው የምሥራቅ አፍሪካ ኃይል ትስስር ጉባዔ ጎን ለጎን የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ስምምነቱ ተፈረመ፡፡

ተዛማጅ ፅሁፎች

በኢትዮጵያና በታንዛኒያ መንግሥታት መካከል ሲካሄድ የቆየው የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ስምምነት ድርድር ተጠናቆ፣ ከረቡዕ ጥር 10 ቀን 2009 ዓ.ም. ጀምሮ በታንዛኒያ አሩሻ ከተማ ሲካሄድ ከቆየው የምሥራቅ አፍሪካ ኃይል ትስስር ጉባዔ ጎን ለጎን የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ስምምነቱ ተፈረመ፡፡

ታንዛኒያ ከሱዳን፣ ከኬንያ፣ ከጂቡቲና ከሶማሌላንድ ቀጥሎ ከኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ለመግዛት የተፈራረመች አምስተኛ አገር ሆናለች፡፡

ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ በአንድ ኪሎ ዋት 11 የአሜሪካ ሳንቲም ክፍያ 400 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ስምምነቱ ተፈርሟል፡፡

በስብሰባው ለመካፈልና የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ስምምነቱን ለመፈረም የተጓዘውን የኢትዮጵያ የልዑካን ቡድን የመሩት የውኃ፣ መስኖና ኤሌክትሪክ ሚኒስትሩ ዶ/ር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ናቸው፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አዜብ አስናቀና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ፕላኒንግ ዳይሬክተር አቶ መኩሪያ ለማን ጨምሮ የተለያዩ የሥራ ኃላፊዎች በልዑካን ቡድኑ ውስጥ ተካተዋል፡፡

የምሥራቅ አፍሪካ የኤሌክትሪክ ኃይል ቋት ለመሆን እየሠራች የምትገኘው ኢትዮጵያ፣ ለታንዛኒያ ኤሌክትሪክ ለማቅረብ ያቀደችው በኬንያ በኩል ነው፡፡

ከደቡብ ክልል ወላይታ ዞን (ሶዶ ከተማ) ጀምሮ እስከ ኬንያ ድረስ 400 ኪሎ ቮልት መሸከም የሚችል ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር እየተገነባ ነው፡፡ ከኢትዮጵያ የሚለቀቀውን ኃይል ታንዛኒያ ከኬንያ ድንበር እንደምትቀበል ተገልጿል፡፡

ኢትዮጵያ ከቡሩንዲ፣ ከሩዋንዳና ከየመን ጋር የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርማ የተለያዩ ድርድሮችን በማካሄድ ላይ ትገኛለች፡፡ የኢትዮጵያ ቀጣዩ ስትራቴጂ በጂቡቲ በኩል የመንን አቋርጦ ለሳዑዲ ዓረቢያ የኤሌክትሪክ ኃይል ለመሸጥ የሚያስችል ፕሮጀክት መጀመር መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ ኢትዮጵያ ከውኃ ብቻ 45 ሺሕ ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም አላት፡፡ 

spot_img
- Advertisement -spot_img

የ ጋዜጠኛው ሌሎች ፅሁፎች

- ማስታወቂያ -

በብዛት ከተነበቡ ፅሁፎች