Saturday, December 9, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ሥነ ፍጥረት​ስደተኛ ወፎች

​ስደተኛ ወፎች

ቀን:

ከአፍሪካ ውጭ ያሉ አገሮች በተለይም አውሮፓ በበረዶ በሚሸፈኑበት በአሁኑ ወቅት ምግብ ለማግኘት የሚቸገሩ ወፎች ይሰደዳሉ፡፡ ቅዝቃዜውን መቋቋም ያልቻሉ ወፎች ስደታቸው በቡድን ሲሆን፣ የብዙዎቹ መዳረሻም አፍሪካ ናት፡፡ የበረራ መስመራቸው ስምጥ ሸለቆ በመሆኑ፣ ብዙዎቹም ኢትዮጵያን ይረግጣሉ፡፡

አብዛኛውን ጊዜያቸውን በስደት የሚያሳለፉት ወፎች ታዲያ የቱሪስት መስብህም ናቸው፡፡ ሰሞኑን የኤደንበርግ ዩኒቨርሲቲ ይዞት የወጣው ጥናት፣ ስደተኛ ወፎች በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት ከዚህ ቀደም ስደት ይጀምሩበት ከነበረው ወቅት ቀድመው መሰደድ ጀምረዋል ብሏል፡፡

በአምስቱ አህጉር በሚገኙና በመቶዎች በሚቆጠሩ የወፍ ዝርያዎች ላይ የተደረገን ጥናት ጠቅሶ ቢቢሲ እንዳሰፈረው፣ የአየር ንብረት ለውጡ ወፎች ምግብም ሆነ የወፍ ጎጆ የሚሠሩበት ቦታ እንዲያጡ ከማድረጉም በተጨማሪ፣ ያለጊዜያቸው እንዲሰደዱ አድርጓል፡፡ ይህ ደግሞ የመፈልፈያ ጊዜያቸው ካለፈ በኋላ ወደ ሥፍራቸው እንዲመለሱ ስለሚያደርግ፣ ወፎቹ እንዲመናመኑ ብሎም እንዲጠፉ ሊያደርግ እንደሚችል ጥናቱ ጠቁሟል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ታዋቂው የኤሌክትሮኒክስ ብራንድ አይቴል የስትራቴጂ ለውጥ አካል የሆነውን አዲስ አርማ እና መለዮ ይፋ አደረገ።

በአለማችን ታዋቂ ከሆኑት የኤሌክትሮኒክስ ብራንዶች መካከል አንዱ የሆነው እና...

የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ጥሪ ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ

ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ የሸገር አነስተኛ የፋይናንስ...

[የክቡር ሚኒስትሩ ጸሐፊ፣ የሌላ ሚኒስትር ጸሐፊ ከሆነችው የቅርብ ወዳጇ ጋር በስልክ እየተጨዋወቱ ነው]

አንቺ ግን ምን ሆነሽ ነው? ጠፋሁ አይደል? ጠፋሁ ብቻ?! ምን ላድርግ ብለሽ...

በሱዳን ላይ ያጠላው የመከፋፈል ዕጣና ቀጣናዊ ተፅዕኖው

የሱዳን ጦርነት ስምንተኛ ወሩን እያገባደደ ይገኛል፡፡ ጄኔራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን...