Wednesday, October 4, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊግሎባል ፈንድ በኢትዮጵያ በነፃነት እንዲንቀሳቀስ የሚፈቅድ ረቂቅ አዋጅ ቀረበ

ግሎባል ፈንድ በኢትዮጵያ በነፃነት እንዲንቀሳቀስ የሚፈቅድ ረቂቅ አዋጅ ቀረበ

ቀን:

ግሎባል ፈንድ በመባል የሚታወቀው ኤድስን፣ ሳንባ ነቀርሳንና ወባን ለመዋጋት በዓለም አቀፍ ደረጃ የተቋቋመው ድርጅት ሀብትን በሚገባ ለመጠቀም፣ ግሎባል ፈንድና እሱ የሚወክላቸው የሥራ ኃላፊው በነፃነት በኢትዮጵያ እንዲንቀሳቀሱ የሚፈቅድ ረቂቅ አዋጅ ለፓርላማ ቀረበ፡፡

የቀረበው ረቂቅ አዋጅ ኢትዮጵያ ያደረገችውን ስምምነት ለማፅደቅ ሲሆን፣ ስምምነቱ በኢትዮጵያ ላይ ከሚጥላቸው ግዴታዎች መካከል ግሎባል ፈንድ የሚሰጣቸው አገልግሎቶችና ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ ማናቸውም ዕቃዎችን፣ መንግሥት ከማንኛውም ዓይነት ግብር ክፍያ ነፃ ማድረግ ይጠበቅበታል፡፡

በሌላ በኩል የግሎባል ፈንድ ሀብትና ንብረት የሆኑ ቁሳቁሶች በየትኛውም ቦታ በማንም ቢያዙ ድርጅቱ ያለውን በሕግ የመጠየቅ ከለላ ካላነሳ በስተቀር በሕግ ሒደት ከመያዝ ነፃ እንደሚሆኑ፣ እንዲሁም በየትኛውም ሥፍራ የሚገኙ የተቋሙ ንብረቶች ከመፈተሽና ከመወረስ ከለላ ይኖራቸዋል፡፡

በሌላ በኩል በግሎባል ፈንድ ውስጥ የሚሠሩ የአባል አገሮች ተወካዮች በሥራ ወቅትና በጉዞ፣ እንዲሁም ጉባዔ በሚደረግበት ጊዜ ለስብሰባ ሲንቀሳቀሱ በፖሊስ ከመያዝና ከመታሰር የመጠበቅ መብት ይሰጣል፡፡ በተጨማሪም በሥራ ምክንያት የሚጠቀሙባቸው ንብረቶች እንዳይያዙና እንዳይበረበሩ፣ ሰነዶችና ደብዳቤዎችን በታሸገ ቦርሳ መቀበል እንዲችሉ፣ ሥራቸው ካበቃም በኋላ ቢሆን በሥራ ላይ እያሉ ከሥራቸው ጋር በተገናኘ ላደረጓቸው ንግግሮችና ለጻፏቸው ጽሑፎች ከሕግ ተጠያቂነት ነፃ እንደሚሆኑ ይገልጻል፡፡ እንዲሁም በዚህ ምክንያት ወደ አገር ውስጥ እንዳይገቡ በኢሚግሬሽን መሥሪያ ቤት ሊከለከሉ እንደማይችል ይገልጻል፡፡

የስምምነቱ መፅደቅ ድርጅቱ ለኢትዮጵያ እያበረከተ ከሚገኘው አስተዋጽኦ አንፃር ከድርጅቱ ጋር ይበልጥ ተቀራርቦ ለመሥራትና መልካም ግንኙነት ለመፍጠር አመቺ ሁኔታን እንደሚፈጥር፣ ከረቂቅ አዋጁ ጋር የተያያዘው ሰነድ ይገልጻል፡፡

የረቂቁ የእንግሊዝኛ ቅጂ እንደሚገልጸው ደግሞ ግሎባል ፈንድ በኢትዮጵያ ባንኮች ውስጥ ማንኛውንም ዓይነት የውጭ ምንዛሪ፣ ወርቅና ፈንዶችን መያዝ ይችላል፡፡ በተጨማሪም በየትኛውም አገር ውስጥ ያለውን የውጭ ገንዘብ ወደ ኢትዮጵያ መላክ፣ ወይም በኢትዮጵያ ገንዘብ የመቀየር መብት እንደሚኖረው ያስረዳል፡፡

ኢትዮጵያ ይህንን ሙሉ በሙሉ የተቀበለች ቢሆንም አፈጻጸሙ ግን በኢትዮጵያ የፋይናንስ ሕጎች መሠረት እንደሚሆን በመግለጽ ተአቅቦ አድርጋለች፡፡ ፓርላማው ረቂቅ አዋጁን ለዝርዝር ዕይታ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ መርቷል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

[ክቡር ሚኒስትሩ ወደ መኖሪያ ቤታቸው ሲገቡ ባለቤታቸው በቴሌቪዥን የሚተላለፈውን ዜና በመገረም እየተመለከቱ አገኟቸው]

ምንድነው እንዲህ ቀልብሽን የሳበው? ስለሰላም ኖቤል ሽልማት ዜና እየተመለከትኩ ነበር። እና...

የወሎ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ መመሥረትና የአማራ ክልል ጥያቄ

አማራ የኢሕአዴግ አንዱ መሥራችና አጋር ከሆነው ብሔረ አማራ ዴሞክራሲያዊ...

የሽንኩርት ዋጋ ሰማይ የነካበት ምክንያት ምንድነው?

ባለፉት ሁለትና ሦስት ሳምንታት የሸማቾችን ኪስ ካስደነገጡ መሠረታዊ ከሚባሉ...

የአዲስ አበባ ንግድ ምክር ቤት ኤግዚቢሽን ማዕከልን እንዲያስተዳድር የተሰጠው ኮንትራት ለምን ተቋረጠ?

በአዲስ አበባ ከተማ ለንግድ ትርዒት ዝግጅት ብቸኛ በመሆን የሚጠቀሰው...