Saturday, June 10, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊትውልደ ኢትዮጵያዊቷ ብሔራዊ ባንክንና የፋይናንስ ድርጅቶችን ከሰሱ

ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ ብሔራዊ ባንክንና የፋይናንስ ድርጅቶችን ከሰሱ

ቀን:

– አክሲዮኖቻቸው ባሉበት እንዲቆዩ ፍርድ ቤት ዕግድ ሰጥቷል

በዜግነት ኢትዮጵያዊ ያልሆኑ ትውልደ ኢትዮጵያውያን በንግድ ባንኮችም ሆነ በኢንሹራንስ ኩባንያዎች የአክሲዮኖች ባለቤት መሆን እንደማይችሉ በወጣው መመርያ ምክንያት፣ ትውልደ ኢትዮጵያዊቷብሔራዊ ባንክን፣ ኅብረት ባንክንና ኅብረት ኢንሹራንስ ኩባንያን ከሰሱ፡፡

በካሊፎርኒያ ነዋሪ የሆኑትና የአሜሪካ ዜግነት ያላቸው ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ ወ/ሪት ሶፊያ በቀለ በጠበቃቸው አቶ ዮሴፍ ኪሮስ አማካይነት ብሔራዊ ባንክን፣ ኅብረት ባንክንና ኅብረት ኢንሹራንስ ኩባንያን በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ አራተኛ ፍትሐ ብሔር ችሎት ከሰዋል፡፡

ግለሰቧ ብሔራዊ ባንክን የከሰሱት ባወጣው መመርያ ኅብረት ባንክና ኅብረት ኢንሹራንስ ኩባንያ ያላቸውን አክሲዮን እንዲመልሱ፣ ካልመለሱ ግን መንግሥት እንደሚወርሰው በመግለጽ በመገናኛ ብዙኃን ጥሪ ማድረጉን በመቃወም ነው፡፡

ከሳሽ የኅብረት ኢንሹራንስ መሥራች የነበሩት አባታቸው እያንዳንዳቸው 1,000 ዋጋ ያላቸው 288 አክሲዮኖችንና እንዲሁም ከኅብረት ባንክ (መሥራች ናቸው) 4,066 አክሲዮኖችን በውርስ እንደተላለፈላቸው በክሳቸው ላይ ገልጸዋል፡፡ የአክሲዮኖቹን ድርሻ ያገኙት ኢትዮጵያዊ ዜግነት ካላቸው አባታቸው መሆኑን የገለጹት ከሳሽ፣ ማንኛውም ሰው በስሙ ተመዝግቦ የሚገኝን ንብረት የመጠቀምና አስፈላጊ በሆነ ጊዜ ለፈለገው ሰው ያለክፍያና ያለምንም ገደብ የማስተላለፍ መብት እንዳለው በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 40(1) እና በፍትሐ ብሔር ሕግ ቁጥር 1205(2) መደንገጉንም አስረድተዋል፡፡

ነገር ግን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ያወጣው መመርያ በሕገ መንግሥቱ የተደነገገውን መሠረታዊ መብት የሚጥስ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ መመርያው ከመውጣቱ በፊት በውርስና በተለያዩ መንገዶች የተላለፉና በከሳሽ ስም የተዘዋወሩ አክሲዮኖች ወደ ኋላ ተመልሰው ሊፈጸሙ እንደማይገባቸውም አስረድተዋል፡፡

በመሆኑም በስማቸው ተመዝግቦ የሚገኘው የአክሲዮን ድርሻ ላይ የብሔራዊ ባንክ መመርያ ተፈጻሚ ሊሆን አይገባም እንዲባልላቸው፣ በጠበቃቸው በኩል ክሳቸውን አቅርበዋል፡፡ በሕግ የተከበሩላቸውን አክሲዮኖች ለፈለጉት ሰው የማስተላለፍ መብታቸውን ተጠቅመው፣ አክሲዮኖቻቸውን ማስተላለፍ እንዲችሉ እንዲወሰንላቸውም አመልክተዋል፡፡

ክሱን የተመለከተው ፍርድ ቤቱ ብሔራዊ ባንክ፣ ኅብረት ባንክና ኅብረት ኢንሹራንስ መልስ እንዲሰጡና በከሳሽ ስም የሚታወቁ አክሲዮኖች ባሉበት እንዲቆዩ ትዕዛዝ ሰጥቶ፣ ክስ ለመስማት ለየካቲት 30 ቀን 2009 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡   

በርካታ ባለድርሻዎች በተለያዩ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ተመሳሳይ ክስ መመሥረታቸውን ምንጮች ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

አያሌ የውኃ “ጠርሙሶች”ን በጫንቃ

መሰንበቻውን በአይቮሪ ኮስት መዲና አቢጃን የምትኖር አንዲት ሴት፣ በሚደንቅ...

ወልቃይትን ማዕከል ያደረገው የምዕራባዊያን ጫና

በትግራይ ክልል የተከሰተው የዕርዳታ እህል ዘረፋ የዓለም አቀፍ ተቋማት...

ከቀጣዩ ዓመት በጀት ውስጥ 281 ቢሊዮን ብሩ የበጀት ጉደለት ነው ተባለ

ለቀጣዩ በጀት ዓመት ከቀረበው 801.65 ቢሊዮን ብር አጠቃላይ በጀት...