Friday, March 24, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክን ከ276.6 ሚሊዮን ብር በላይ በማስመዝበር የተጠረጠሩ ኃላፊዎች ታሰሩ

ኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክን ከ276.6 ሚሊዮን ብር በላይ በማስመዝበር የተጠረጠሩ ኃላፊዎች ታሰሩ

ቀን:

  በኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክ የፋይናንስ የሥራ ሒደት ዳይሬክተርና የደንበኞች ግንኙነት አስተዳደር የሥራ ሒደት ዳይሬክተር፣ ባንኩን ከ276.6 ሚሊዮን ብር በላይ በማስመዝበር ተጠርጥረው ታሰሩ፡፡

          ተጠርጣሪዎቹ የባንኩ ኃላፊዎች አቶ ሳሙኤል ግርማ ደሴና አቶ በለጠ ዋቅቤካ ሂርጳ ናቸው፡፡ የተጠረጠሩበትን ወንጀል ፈጽመዋል የተባለው በባንኩ የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ላይ መሆኑን፣ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል ምርመራ ቢሮ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሁለተኛ ወንጀል ችሎት አስረድቷል፡፡

ሁለቱም ተጠርጣሪዎች በቅርንጫፉ ኃላፊ ሆነው በሚሠሩበት ወቅት በቅርንጫፉ ‹አካውንት ሪሲቨብል›፣ ‹ኤክስፖርት ሴትልመንት አካውንት› የሚባል ሒሳብ ከባንኩ ዕውቅና ውጪ በመክፈትና ከሌሎች ግለሰቦች ጋር በመመሳጠር፣ 276,675,572 ብር ባንኩ እንዲመዘበር ማድረጋቸውን ፖሊስ ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል፡፡

በመሆኑም ከጥር 1 ቀን 2009 ዓ.ም. ጀምሮ በቁጥጥር ሥር አውሎ እየመረመራቸው እንደሚገኝ ፖሊስ በማስረዳት፣ የወንጀል አፈጻጸሙ ውስብስብና አስቸጋሪ መሆኑን በመግለጽ ለተጨማሪ ምርመራ 14 ቀናት እንዲፈቀድለት ፍርድ ቤቱን ጠይቆ ተፈቅዶለታል፡፡

 

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሚያከብሯቸው አንድ የቀድሞ ጉምቱ ፖለቲከኛ ስልክ ተደውሎላቸው እያወሩ ነው]

አንዳንድ ነገሮች ቢያሳስቡኝ ነው ቀጠሮ ሳልይዝ ላወራህ የፈለኩት ክቡር...

የትግራይ ክልል የሽግግር አስተዳደር ምሥረታና የሰላም ስምምነቱ ሒደት

በትግራይ ክልል ጊዜያዊ የሽግግር መንግሥት ለመመሥረት ደፋ ቀና እየተባለ...

ጥራዝ ነጠቅነት!

ከሜክሲኮ ወደ ጀሞ እየሄድን ነው፡፡ የተሳፈርንበት አሮጌ ሚኒባስ ታክሲ...