Sunday, April 2, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናበደቡብ ኦሞ ከ12 በላይ ሰዎች ተገደሉ

በደቡብ ኦሞ ከ12 በላይ ሰዎች ተገደሉ

ቀን:

በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን ሰኞ ማታ በተከሰተ ግጭት ከ12 በላይ ሰዎች ሲሞቱ ከ26 የሚበልጡ ሰዎች ደግሞ ጉዳት ደረሰባቸው፡፡

የግጭቱ መነሻ የቦዲ ብሔረሰብ አባል የሆነ ግለሰብ በመኪና ተገጭቷል በሚል ምክንያት ሲሆን፣ የብሔረሰቡ አባላት ያገኟቸውን መኪናዎች በሙሉ ሲያጠቁ እንደነበር ለማወቅ ተችሏል፡፡

በተፈጠረው ግጭት ከተገደሉት ውስጥ ብዙዎቹ በአካባቢው ባሉ የግንባታ ሥራ ተቋራጭ ድርጅቶች ውስጥ በሾፌርነት ሲያገለግሉ የነበሩ እንደሆኑ፣ እንዲሁም ነዋሪነታቸውም ኃይል ውሃ በተባለ ሥፍራ እንደነበረም ለማወቅ ተችሏል፡፡

በግጭቱ ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች በሶዶ ክርስቲያን ሆስፒታልና በጂንካ ሆስፒታል የሕክምና ዕርዳታ እየተደረገላቸው እንደሚገኝ የአካባቢው ምንጮች ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

የደቡብ ክልል የሕዝብ ግንኙነትና የሚዲያ ዳይሬክተር አቶ ሲሳይ በቀለ፣  << የተፈጠረውን ግጭት ሰምተን እየተከታተልነው ነው፣ >> ሲሉ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

አካባቢው አሁን እየተረጋጋና ወደ ቀድሞው ሁኔታ እየተመለሰ እንደሆነም አቶ ሲሳይ አክለዋል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ኦቲዝምን ለመቋቋም በጥምረት የቆሙት ማዕከላት

ከኦቲዝም ጋር የሚወለዱ ልጆች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ...

አወዛጋቢው የወልቃይት ጉዳይ

የአማራና ትግራይ ክልሎችን እያወዛገበ ያለው የወልቃይት ጉዳይ ዳግም እየተነሳ...

ተጠባቂው የቴሌኮም ኦፕሬተሮች የውድድር መለኪያ የሆነው የሞባይል ገንዘብ ዝውውር በኢትዮጵያ

የሞባይል ገንዘብ ዝውውር የሞባይል ስልክን በመጠቀም ሊገኙ የሚችሉ የፋይናንስ...

የአማራና ደቡብ ክልሎች ለሠራተኛ ደመወዝ መክፈል መቸገራቸውን የፓርላማ አባላት ተናገሩ

በአማራና በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልሎች የሚገኙ የመንግሥት ተቋማት...