Sunday, June 4, 2023
- ማስታወቂያ -
- ማስታወቂያ -

የኮንስትራክሽን ኢንስቲትዩት የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅዱን ይፋ አደረገ

- ማስታወቂያ -

ተዛማጅ ፅሁፎች

 –  የመንግሥት ፕሮጀክቶችን ለመቆጣጠርና አዲት ለማድረግ ያቀረበው ጥያቄ ውድቅ ተደርጓል

ከተመሠረተ ሁለት ዓመት ከመንፈቅ ያስቆጠረው የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ፕሮጀክት ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት ለአምስት ዓመታት የሚመራበትን ስትራቴጂካዊ ዕቅድ ይፋ አደረገ፡፡ ዕቅዱ ምንም እንኳ ረቂቅ የዕቅዱ ሰነድ ባለፈው ዓመት ቢዘጋጅም ማሻሻዎች ማድረግ በማስፈልጉ ያንን በማካተት ለሚለመከታቸው ባለድርሻ አካላት የቀረበው ታኅሳስ 26 ቀን 2009 ዓ.ም. ነበር፡፡

ኢንስቲትዩቱ ለመጪዎቹ አምስት ዓመታት በኮንስትራክሽን ፕሮጀክት ማኔጅመንት ዘርፍ የሚተገብራቸውን ዋና ዋና ተግባራት ያካተተበት ስትራቴጂካዊ ዕቅድ፣ ትኩረት ከሰጠባቸው መስኮች መካከል በዘርፉ ያለውን የሰው ኃይል አቅም መገንባት አንዱ ነው፡፡

የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ዮሴፍ ብሩ የስትራቴጂክ ዕቅዱን ረቂቅ ሰነድ፣ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ዘርፍ ቋሚ ኮሚቴ አባላት፣ ከፈደራልና ከክልል መንግሥት ለተውጣጡ ባለድርሻዎች በማቅረብ ውይይት እንዲካሄድበት አድርገዋል፡፡

ዋና ዳይሬክትሩ ባቀረቡት ዕቅድ ውስጥ ለኢንስቲትዩቱ እንዲሰጥ ከጠየቋቸው መካከል አንዱና ዋናው አስገዳጅ የሕግ ማዕቀፍ እንዲሰጠው የሚለው ይጎላል፡፡ እንደ ዶ/ር ብሩ ማባብራሪያ ከሆነ፣ ኢንስቲትዩቱ የሕግ ሥልጣን ተሰጥቶት በአስገዳጅነት የመንግሥትን ፖሊሲ ማስፈጸም እንዳይችል የሚገድበው፣ የተቋቋመበት ደንብ እንዲሻሻልም ጠይቀዋል፡፡ ዶ/ር ዮሴፍ ባቀረቡት ጥያቄ መሠረት፣ የኮንስትራክሽን ሚኒስቴር በተለይ የመንግሥት የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶችን የአፈጻጸም ሒደት ለመገምገምና ለመቆጣጠር እንዲሁም ኦዲት ለማድረግ የሚያስችለው የሕግ ማዕቀፍ ሊሰጠው ይገባል፡፡

ይሁንና ይህ ጥያቄ በሕግ የማፈቀድለት ከሆኑ ባሻገር የኢንስቲትዩቱ ኃላፊነት ባለመሆኑ፣ የመንግሥት ፕሮጀክቶችን የአፈጻጸም ሒደት በአስገዳጅ የሕግ ማዕቀፍ የመገምገምም ሆነ ኦዲት የማድረግ ጥያቄው በሚኒስቴሩ ተቀባይነት እንዳላገኘ ታውቋል፡፡ የኮንስትራክሽን ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ገብረመስቀል ጫላ ከሪፖርተር ተጠይቀው እንዳብራሩት፣ ኢንስቲትዩቱ በዚህ ደረጃ ለመንቀሳቀስ የሚስችለው የሕግ ማዕቀፍ ስለሌለው ጥያቄው አልተስተናገደም፡፡

በአምስት ዓመቱ የኢንስቲትዩቱ ስትራቴጂክ ዕቅድ ውስጥ በአገሪቱ የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ውስጥ ከሚታዩ አንኳር አንኳር ችግሮች መካከል ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቅ መሆኑ፣ የጥራት ችግሮች የተበራከቱበት መሆኑ፣ የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ ውስጥ የማይጠናቀቁበት መሆኑ፣ የግንባታ ፍላጎትና አቅም አለመጣጣማቸው እንዲሁም ከፍተኛ የሰለጠነ የሰው ኃይል እጥረት መኖሩ የሚጠቀሱት ናቸው፡፡ ከዚህ ባሻገር በኮንስትራክሽን ዘርፍ ውስጥ የሚታየው ሙስናም ሥር የሰደደ ከመሆኑም ባሻገር በተለይ በግዥ ሒደት የሚታየው ሕገወጥ አሠራር ኢንስቲትዩቱ መፍትሔ እንደሚፈልግላቸው ይጠበቃል፡፡

እንደ ዶ/ር ዮሴፍ ማብራሪያ ከሆነ የኮንስትራክሽን ፕሮጀክት ማኔጀመንት ሙያ በአገሪቱ ብዙም የማይታወቅ በመሆኑ ይህንን ከመቅረፍ ጀምሮ፣ ከተመራቂ ተማሪዎች እስከ ልምድ ያካበቱት ድረስ የሙያ ምዘናና የሚደረግባች አሠራሮች እንደሚኖሩ ይጠበቃል፡፡ በመሆኑም የልቀት ማዕከል ለማቋቋም ማቀዱንና በክልሎችም ቅርንፋፍ ጽሕፈት ቤቶችን በመክፈት የቴክኒክና የክህሎት ሥልጠና ከመስጠት ባሻገር ለፕሮጀክቶች የማማከር ድጋፍና መሠል ሥራዎችን የማከናወን ተልዕኮ እንደሚኖረውም አብራርተዋል፡፡

ባለፉት ሁለት ዓመታት ጊዜ ውስጥ ካከናወናቸው ተግባራት መከካል ለአዲስ አበባ ቤቶች ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ሲሰጥ የቆየው የዲዛይን፣ የግብዓት አጠቃቀምና መሰል ሥራዎች እንደሚጠቀሱለት ሚኒስትር ዴኤታው አቶ ገብረ መስቀል አስታውሰዋል፡፡    

spot_img
- Advertisement -spot_img

የ ጋዜጠኛው ሌሎች ፅሁፎች

- ማስታወቂያ -

በብዛት ከተነበቡ ፅሁፎች