Friday, December 8, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊበድርቅ በተጎዱ አካባቢዎች ለ2.8 ሚሊዮን ሕፃናት የትምህርት መሣሪያ ድጋፍ ተደረገ

በድርቅ በተጎዱ አካባቢዎች ለ2.8 ሚሊዮን ሕፃናት የትምህርት መሣሪያ ድጋፍ ተደረገ

ቀን:

የአሜሪካው ዓለም አቀፍ የልማት ድጋፍ ኤጀንሲ (ዩኤስኤአይዲ) በድርቅ በተጎዱት አፋር፣ አማራ፣ ሐረሪ፣ ኦሮሚያ፣ ደቡብ በኢትዮጵያ ሶማሌና ትግራይ ክልሎች፣ ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር፣ ባሉ ወረዳዎች ለሚገኙ 2.8 ሚሊዮን ለሚሆኑ ሕፃናት ተማሪዎች 8.2 ሚሊዮን ደብተሮችንና 5.5 ሚሊዮን እስክርቢቶና እርሳሶችን መስጠቱን የአሜሪካ ኤምባሲ ለሪፖርተር በላከው መግለጫ አስታውቋል፡፡

የድጋፉ ዓላማ በአገሪቱ ከባድ በተባለው ድርቅ ተጋላጭ የሆኑ ሕፃናት የመማር መብት እንዳይጓደል መሆኑም በመግለጫው ተጠቅሷል፡፡ እነዚህን የትምህርት ቁሳቁሶች አገር በቀሉ የኅትመት ድርጅት የካቲት ወረቀቶች እንዲሁም በአሜሪካ የሚገኙ አነስተኛ የቢዝነስ ተቋማት እንዲያቀርቡ መደረጉም ተገልጿል፡፡ የደብተር፣ የእስክርቢቶና እርሳስ ድጋፍ የተደረገላቸው ከአንደኛ እስከ ስምንተኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎች ሲሆኑ ዕርዳታዎቹ ለተማሪዎቹ ይደርሱ ዘንድ የትምህርት ሚኒስቴርና የክልል ትምህርት ቢሮዎች ኃላፊነታቸውን እንደተወጡ ተጠቁሟል፡፡

የተደረገው የትምህርት መሣሪያ ድጋፍ በድርቅ ተፅዕኖ ተቋርጦ የነበረው ትምህርት እንዲቀጥል ሕፃናቱም ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱ ማስቻሉን የዩኤስኤአይዲ ኢትዮጵያ ሚሽን ዳይሬክተር ሌዝሊ ሪድ ተናግረዋል፡፡ 

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ታዋቂው የኤሌክትሮኒክስ ብራንድ አይቴል የስትራቴጂ ለውጥ አካል የሆነውን አዲስ አርማ እና መለዮ ይፋ አደረገ።

በአለማችን ታዋቂ ከሆኑት የኤሌክትሮኒክስ ብራንዶች መካከል አንዱ የሆነው እና...

የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ጥሪ ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ

ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ የሸገር አነስተኛ የፋይናንስ...

[የክቡር ሚኒስትሩ ጸሐፊ፣ የሌላ ሚኒስትር ጸሐፊ ከሆነችው የቅርብ ወዳጇ ጋር በስልክ እየተጨዋወቱ ነው]

አንቺ ግን ምን ሆነሽ ነው? ጠፋሁ አይደል? ጠፋሁ ብቻ?! ምን ላድርግ ብለሽ...

በሱዳን ላይ ያጠላው የመከፋፈል ዕጣና ቀጣናዊ ተፅዕኖው

የሱዳን ጦርነት ስምንተኛ ወሩን እያገባደደ ይገኛል፡፡ ጄኔራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን...