Friday, December 8, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርትዳይመንድ ሊግ የሽልማት መጠኑን ከፍ አደረገ

ዳይመንድ ሊግ የሽልማት መጠኑን ከፍ አደረገ

ቀን:

ዓመታዊ የዳይመንድ ሊግ የአትሌቲክስ ውድድር ለአሸናፊዎች የሚሰጠውን የሽልማት መጠን ከፍ ማድረጉን የውድድር አዘጋጁ በድረ ገጹ አስታውቋል፡፡ እ.ኤ.አ. በ2017 ለሚደረጉት ዓለም አቀፍ የዳይመንድ ሊግ ውድድሮች 3.2 ሚሊዮን ዶላር መመደቡን መረጃው ያመለክታል፡፡

በቀጣይ ለማከናወን ከታቀዱት ውድድሮች ተወዳዳሪዎች በሚያገኙት ነጥብ የሚመዘኑ ሲሆን፣ በመጀመሪያ የአይኤኤፍ ዳይመንድ ሊግ በ32 የውድድር ዓይነቶች ለሚወዳደሩና ውጤታማ ለሚሆኑ 100,000 ዶላር፣ ሁለት የፍጻሜ ውድድር ላይ ለሚያሸንፉ 50 ሺሕ ዶላር ተዘጋጅቷል፡፡

በውድድሩ ላይ የሚያሳዩት ብቃት ከግምት ውስጥ በማስገባትም ተጨማሪ ጉርሻ እንደተዘጋጀ ተገልጿል፡፡ እንደ ዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ማኅበር አይኤኤኤፍ ፕሬዚዳንት ሰባስትያንኮ አስተያየት ከሆነ፣ ‹‹ምንም እንኳ የዳይመንድ ሊግን ውድድር ከጀመረ ሰባት ዓመት ብቻ ቢሆንም የሽልማት ክፍያን ከፍ በማድረግ በቀጣይ ውድድሩ ወደ ተሻለ ደረጃ ለማድረስ መንገድ ይከፍታል፤›› በማለት ተናግረዋል፡፡

በ32 የውድድር ዓይነቶች ላይ አሸናፊ የሚሆኑ አትሌቶች ከ50 ሺሕ እስከ 2000 ዶላር ድረስ እንደየደረጃቸው መሸለም እንደሚችሉ በድረ ገጹ ተቀምጧል፡፡ በሜዳ ተግባር ውድድር ላይ ለሚሳተፉ ተወዳዳሪዎች ከዚህ ቀደም ሦስት የሙከራ ጊዜ የሚሰጣቸው የነበረ ሲሆን፣ በዘንድሮ ውድድር ግን ምርጥ አራቶች ብቻ ሦስት የድጋሚ ሙከራ እንደሚሰጣቸው ተጠቁሟል፡፡

የአይኤኤኤፍ ዳይመንድ ሊግ ዓመታዊ የአትሌቲክስ ውድድር ሲሆን፣ አትሌቶች በግላቸው በመሳተፍ ከፍተኛ ገንዘብ የሚሰበስቡበት ውድድር ነው፡፡ እ.ኤ.አ. በ2010 የጀመረው የውድድር መርሐ ግብር በአውሮፓ፣ እስያ፣ ሰሜን አሜሪካና አፍሪካ ላይ ይካሄዳል፡፡

በ2017 የውድድር ፕሮግራምም 14 የዳይመንድ ሊግ ሻምፒዮናዎች በተለያዩ የዓለም አገሮች ለማከናወን ታቅዷል፡፡ ኢትዮጵያውያኑ አትሌቶች ገንዘቤ ዲባባ፣ አልማዝ አያና፣ ታምራት ቶላ፣ ሐጎስ ገብረሕይወትን ጨምሮ በርካታ አትሌቶች ተሳታፊ ይሆናሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ እንደ 2015 የዳይመንድ ሊግ የክፍያ መረጃ መሠረት ከኢትዮጵያ አትሌቶች በዳይመንድ ሊግ ውድድር ላይ ተሳትፎ ከፍተኛ ተከፋይ በመሆን 14ኛ ደረጃን በመያዝ ገንዘቤ ዲባባ ቀዳሚ ነች፡፡ 

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ታዋቂው የኤሌክትሮኒክስ ብራንድ አይቴል የስትራቴጂ ለውጥ አካል የሆነውን አዲስ አርማ እና መለዮ ይፋ አደረገ።

በአለማችን ታዋቂ ከሆኑት የኤሌክትሮኒክስ ብራንዶች መካከል አንዱ የሆነው እና...

የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ጥሪ ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ

ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ የሸገር አነስተኛ የፋይናንስ...

[የክቡር ሚኒስትሩ ጸሐፊ፣ የሌላ ሚኒስትር ጸሐፊ ከሆነችው የቅርብ ወዳጇ ጋር በስልክ እየተጨዋወቱ ነው]

አንቺ ግን ምን ሆነሽ ነው? ጠፋሁ አይደል? ጠፋሁ ብቻ?! ምን ላድርግ ብለሽ...

በሱዳን ላይ ያጠላው የመከፋፈል ዕጣና ቀጣናዊ ተፅዕኖው

የሱዳን ጦርነት ስምንተኛ ወሩን እያገባደደ ይገኛል፡፡ ጄኔራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን...