Friday, December 8, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርትየቴኳንዶ አሶሴሽን ወደ ብሔራዊ ፌዴሬሽን አደገ

የቴኳንዶ አሶሴሽን ወደ ብሔራዊ ፌዴሬሽን አደገ

ቀን:

የኢትዮጵያ ኢንተርናሽናል ቴኳንዶ አሶሴሽን ወደ ፌዴሬሽን ማደጉን ተከትሎ በክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ተቀባይነት እያገኘ መምጣቱ ተገለጸ፡፡

ቀድሞ በፌዴራል ደረጃ ተቀምጦ የነበረውና በማስተር ኪሮስ ገብረመስቀል ሲመራ የቆየው የኢትዮጵያ ኢንተርናሽናል ቴኳንዶ አሶሴሽን፣ ከ36 በላይ ሕጋዊ የሆኑ ውድድሮች ላይ ይሳተፉ የነበሩ ክለቦች ያሉት ማኅበር በመሆኑ፣ ወደ ፌዴሬሽን ደረጃ በማደግ ኢንተርናሽናል የኢትዮጵያ ቴኳንዶ ፌዴሬሽን መሆን ችሏል፡፡

ሐሙስ ኅዳር 29 ቀን 2009 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ኢንተርናሽናል ቴኳንዶ ፌዴሬሽን ስር ሲመራ የነበረው የአዲስ አበባ ቴኳንዶ አሶሴሽን በፌዴሬሽን ደረጃ መቀመጥ መቻሉን አሳውቋል፡፡

በዚህም መሠረት ከክልል የሶማሌና አማራ ክልሎችን ተከትሎ በፌዴሬሽኑ ስር ለመተዳደር ፈቃደኝነቱን የገለጸው የአዲስ አበባ ቴኳንዶ አሶሴሽን መጠሪያውን በመቀየር የአዲስ አበባ ኢንተርናሽናል ቴኳንዶ ፌዴሬሽን በሚል እንደሚጠራ ተገልጿል፡፡ በዕለቱ በተደረገው የማስተዋወቅ ሥነ ሥርዓት ላይም የመተዳደሪያና የመቋቋሚያ ደንበ የፀደቀ ሲሆን፣ የጽሕፈት ቤት ኃላፊና ፕሬዚዳንት ምርጫ አከናውኗል፡፡

ከ1997 ዓ.ም. ጀምሮ የተለያዩ የቴኳንዶ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎችን በአሶሴሽን ደረጃ ሲያከናውን የቆየው የኢትዮጵያ ኢንተርናሽናል ቴኳንዶ ፌዴሬሽን፣ የኢትዮጵያ ፌዴሬሽን ፈቃድን ለማግኘት ጥያቄውን ከሁለት ዓመት በፊት አቅርቦ በ2009 ዓ.ም. መጀመሪያ ወር ከወጣቶችና ስፖርት ሚኒስቴር ተቀባይነት ማግኘቱን ፕሬዚዳንቱ ማስተር ኪሮስ ገብረመስቀል ለሪፖርተር አብራርተዋል፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ ከ45 ክለቦች በላይ፣ በኦሮሚያ 75 ክለቦች እንዲሁም በተመሳሳይ ሁኔታ በአማራ፣ ትግራይና ደቡብ ክልሎች ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ክለቦች መኖራቸውን ተጠቁሟል፡፡

በማኅበር ስር ሆኖ የተለያዩ ውድድሮችና ሥልጠናዎችን ሲያከናውን የነበረው የኢትዮጵያ ኢንተርናሽናል ቴኳንዶ ፌዴሬሽን፣ ‹‹ከአምስት ክልሎች በላይ ስፖርቱን በማስፋፋቱና የተለያዩ ውድድሮችን በማድረግ ወደ ፌዴሬሽን ማደግ ችሏል›› በማለት ፕሬዚዳንቱ አብራርተዋል፡፡ በፌዴሬሽን ደረጃ መቀመጡ የራሱ ሥራ አስፈጻሚ ተመድቦለት፣ ዓመታዊ በጀት ተወስኖለትና የውድድር ቁጥር በመጨመር በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪዎችን ማፍራት እንደሚቻልም ተገልጿል፡፡

በተጨማሪም በፌዴሬሽን ስር መሆኑ ዓለም አቀፍ ግንኙነትን ከማጠናከር አንፃር ከቁሳቁስና የገንዘብ ድጋፍን ለማግኘት ጠቀሜታ እንዳለው ተጠቁሟል፡፡

የባለሙያ እጥረትን በተመለከተ ለተነሳው ጥያቄ የጥራት ችግር ካልሆነ በስተቀር እምብዛም እንደ ችግር የሚነሳ ጉዳይ እንዳልሆነ ማስተር ኪሮስ አብራርተዋል፡፡

በአሶሴሽን ደረጃ ተዋቅሮ እንቅስቃሴውን ከጀመረ 11 ዓመታትን ያስቆጠረው የኢትዮጵያ ኢንተርናሽናል ቴኳንዶ ፌዴሬሽን፣ ሦስት ኢንተርናሽናል ውድድሮች ላይ መሳተፍ ሲችል በኢትዮጵያ ደግሞ አንድ የአፍሪካ ሻምፒዮን ማዘጋጀት ችሏል፡፡

በሻምፒዮናው ላይም የህንድ፣ አሜሪካና እንግሊዝ በተጋባዥነት ተገኝተው ከመሳተፋቸው ባሻገር የቁሳቁስ ድጋፍ ማበርከት መቻላቸው ጭምር ተጠቁሟል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ታዋቂው የኤሌክትሮኒክስ ብራንድ አይቴል የስትራቴጂ ለውጥ አካል የሆነውን አዲስ አርማ እና መለዮ ይፋ አደረገ።

በአለማችን ታዋቂ ከሆኑት የኤሌክትሮኒክስ ብራንዶች መካከል አንዱ የሆነው እና...

የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ጥሪ ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ

ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ የሸገር አነስተኛ የፋይናንስ...

[የክቡር ሚኒስትሩ ጸሐፊ፣ የሌላ ሚኒስትር ጸሐፊ ከሆነችው የቅርብ ወዳጇ ጋር በስልክ እየተጨዋወቱ ነው]

አንቺ ግን ምን ሆነሽ ነው? ጠፋሁ አይደል? ጠፋሁ ብቻ?! ምን ላድርግ ብለሽ...

በሱዳን ላይ ያጠላው የመከፋፈል ዕጣና ቀጣናዊ ተፅዕኖው

የሱዳን ጦርነት ስምንተኛ ወሩን እያገባደደ ይገኛል፡፡ ጄኔራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን...