Monday, March 20, 2023
- ማስታወቂያ -
- ማስታወቂያ -

የቀድሞ የኮንስትራክሽንና ቢዝነስ ባንክ ፕሬዚዳንት የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ምክትል ፕሬዚዳንት ሆኑ

- ማስታወቂያ -

ተዛማጅ ፅሁፎች

የኮንስትራክሽንና ቢዝነስ ባንክ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር ከመዋሃዳቸው በፊት የኮንስትራክሽንና ቢዝነስ ባንክ ፕሬዚዳንት በመሆን ሲያገለግሉ የነበሩት አቶ ኃይለ ኢየሱስ በቀለ፣ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ምክትል ፕሬዚዳንት ሆነው መሰየማቸው ተገለጸ፡፡

ምንጮች እንደገለጹት የኮንስትራክሽንና ቢዝነስ ባንክና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሲዋሀዱ አቶ ኃይለ ኢየሱስ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የፋይናንስ ምክትል ፕሬዚዳንት ሆነው ለወራት ሲሠሩ ከቆዩ በኋላ፣ ኃላፊነታቸውን ለቀው በሥራ ገበታ ላይ እንዳልነበሩ ምንጮች ገልጸዋል፡፡  

ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ላይ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ምክትል ፕሬዚንዳትና አማካሪ ሆነው እንዲያገለግሉ መሰየማቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡ አቶ ኃይለ ኢየሱስ ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ ልማት ባንክን ለስምንት ዓመታት በፕሬዚዳንትነት የመሩ ናቸው፡፡

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ መዋቅር ሁለት ምክትል ፕሬዚዳንቶች ሲኖሩት፣ የአቶ ኃይለ ኢየሱስ ሹመት ባንኩ ሦስት ምክትል ፕሬዚዳንቶች እንዲኖሩት አድርጓል፡፡ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በቅርቡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዥ የነበሩት   አቶ ጌታሁን ናና በፕሬዚዳንትነት እንደሰየሙለት ይታወሳል፡፡

spot_img
- Advertisement -spot_img

የ ጋዜጠኛው ሌሎች ፅሁፎች

- ማስታወቂያ -

በብዛት ከተነበቡ ፅሁፎች